“ላገዛችሁኝ በሙሉ እግዜር ይስጥልኝ”
ጋዜጠኛ ምስጋናው ታደሰ
*…. ጋዜጠኛ ምስጋናው ታደሰ ወደ ሀረር አቅንቷል.. *…..ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል…
“የጋዜጠኛ ምስጋናው ታደሰ ህይወትን ለመታደግ በተደረገው ርብርብ ህዝቡ ለስፖርት ጋዜጠኞች ያለውን ፍቅር አይተንበታል” ሲል የገቢ ማሰባሰቢያ ኮሚቴው አስታወቀ።
የኮሚቴው አባላት የሆኑት ጋዜጠኛ ንዋይ ይመር፣ ጋዜጠኛ ኑራ ኢማምና ጋዜጠኛ ስዩም ፍቃዱ ዛሬ ጠዋት በጁፒተር ሆቴል በሰጡት መግለጫ “ህብረተሰቡ ሙያችንን አክብረን እንስራ እንጂ ለኛ ያለውን
ትልቅ ክብር አይተንበታል ለዚህም እናመሰግናለን” ብሏል።
- ማሰታውቂያ -
በገቢ ማሰባሰቢያ ሂደቱ ላይ ትብብር ያደረጉ የረዱ ወገኖችን ያመሰገነው ኮሚቴው በተለይ በግል የፌስቡክ ገጻቸው ላይ የገቢ ማሰባሰቢያ ያደረጉትን ጋዜጠኛ ታሜሩ አለሙና ጋዜጠኛ አሸናፊ ዘለሌ ለገቢ ማሰባሰቢያ ጥያቄ ወደ ተቋማት ለልመና እንዳንሄድ አድርገውናል ከገቢው 3/4ኛው የተገኘው በሁለቱ የቀጥታ የገቢ ማሰባሰቢያ ስራ ምክንያት ነው ” ሲሉ አመስግነዋል።
ኮሚቴው እንደተናገረው የስፖርት ቤተሰብ የሆነው ሄኖክ ሄነሪ ፣ ከሲያትል ታምራት አበራ ፣ አንዳርጋቸው ሰለሞን፣ አቶ ሸዋረጋ፣ ጋዜጠኛ ይስሃቅ በላይ፣ የፊደል ባለቤት ኤፍሬም ኤርሚያስ እንደ ተቋም 50 ሺህ ብር የረዳው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ገቢ ማሰባሰቢያው እንዲሳካና 2 ሚሊዮን 244 ሺህ
3 12 ገቢ እንዲገኝ አድርገዋል በማለት አመስግኗል።
ኮሚቴው እንደገለጸው በመቅረዝ ሆስፒታል የ10 ቀናት ቆይታ ከ100 ሺህ ብር በላይ ወጪ መደረጉን አስረድቶ
የጋዜጠኛ ምስጋናው ህመም የቤተሰብ ክትትል ስለሚያስፈልገው እናትና አባቱም እኛ ጋር ሆኖ ክትትል ለማድረግ እንወስደው በማለታቸውና ሀኪሞችም በመፍቀዳቸው ዛሬ ጠዋት ከእናትና አባቱ ጋር ወደ ሀረር
ማቅናቱን አስረድተዋል።
“በግለሰብ ደረጃ ከ5 ብር እስከ መቶ ሺህ ብር ገቢ ተገኝቷል ይሄ መላው ህብረተሰብ ጋር ተደራሽ መሆኑን አሳይቷል ለዚህ ደግሞ ቅስቀሳ ያደረጉ የመገናኛ ብዙሃን ባልደረቦቻችንን እናመሰግናለን” ያሉት የኮሚቴው አባላት ጋዜጠኛ ንዋይ ይመር፣ ጋዜጠኛ ኑራ ኢማምና ጋዜጠኛ ስዩም ፍቃዱ በአጠቃላይ ለተደረገው ድጋፍ ርዳታና ርብርብ መላው ህብረተሰቡን አመስገግነዋል።