By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በናማዎቹን አሸንፈዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ባህርዳር ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በናማዎቹን አሸንፈዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 1 year ago
Share
SHARE

 

በስምንተኛው ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሶስተኛ ቀን ጨዋታ ባህርዳር ከተማ የተመስገን ዳናዉን ኢትዮጵያ ቡና 3ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በአንድ ነጥብ ብቻ ተበላልጠው አምስተኛ እና ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኙ የነበሩት ሁለቱ ክለቦች በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ተመጣጣኝ ፉክክር ሲያደርጉ የተስተዋለ ቢሆንም በሙከራ ረገድ ግን የጣና ሞገዶቹ የተሻሉ ነበሩ ማለት ይቻላል።

በዚህም በጨዋታዉ የመጀመሪያ 15 ያህል ደቂቃዎች በዱሬሳ ሹቤሳ ፣ ፍፁም ጥላሁን እና ኦሴ ማውሊ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ማድረግ የቻሉት ባህርዳር ከተማዎች በ22ኛዉ ደቂቃ ላይ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ማስቆጠር ችለዋል።

- ማሰታውቂያ -

በዚህም የመስመር ተጫዋቹ ዱሬሳ ሹቤሳ በግራ መስመር በኩል ኳሷን ገፍቶ ወደ ሳጥን ዉስጥ ሲገባ ጥፉት ቢሰራበትም ኳሷን ኦሴ ማዉሊ በፍጥነት ለፋአድ ፈረጃ አቀብሎት ፉአድ ከሳጥን ዉጭ በቀጥታ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ ካስቆጠሩ በኋላ የተረጋጋ የጨዋታ መንገድን የመረጡት ባህርዳር ከተማዎች በድጋሚ መሪነታቸዉን ወደ ሁለት ከፍ ማድረጉ የሚችሉበን ዕድል ማግኘት ችለዉ የነበረ ቢሆንም ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል። በዚህም በ35ኛዉ ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር በኩል የተቀበለዉን ኳስ ፉአድ ፈረጃ ከርቀት ቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ እንደምንም አዉጥቶበታል።

በተቃራኒዉ ቡናማዎቹ ምንም እንኳን በሂደት የኳስ ቁጥጥር የበላይነቱን በመዉሰድ ጥሩ መንቀሳቀስ ቢችሉም ይህ ነዉ ተብሎ የሚጠቀስ የግብ ሙከራ ማድረግ ሳይችሉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስ ኢትዮጵያ ቡናዎች በመጠኑም ቢሆን ተሻሽለው ወደ ሜዳ ቢመለሱም በተከላካዮች ስህተት ሁለተኛ ግብ ለማስተናገድ ተገደዋል።

በዚህም በ49ኛዉ ደቂቃ ላይ ከመሀል ሜዳ በረጅሙ የተሻገረዉን ኳስ የቡናዉ ተከላካይ ወልደአማኑኤል ጌቱ መቆጣጠር ባለመቻሉ ምክንያት አጠገቡ ይገኝ የነበረዉ ፍፁሙ ኳሷን ገፍቶ ሳጥን ዉስጥ ከገባ በኋላ ወደ ግብነት በመቀየር የባህርዳር ከተማን መሪነት ወደ ሁለት ለዜሮ ከፍ ማድረግ ችሏል።

በተጨማሪም በ62ኛዉ ደቂቃ ላይ ክዋኩ ዱሬሳ ሹቤሳ ላይ የሰራዉን ጥፋት ተከትሎ የተሰጠውን ቅጣት ምት ፍፁም ጥላሁን ቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በጥቂቱም ቢሆን ጫና መፍጠር ችለዉ የነበሩት ቡናማዎቹ በ70ኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም የጣና ሞገዶቹ ተከላካይ ፈቱዲን ጀማል ጫላ ተሽታ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተሰጠውን ፍፁም ቅጣት ምት ኤርትራዊው አማካይ ሮቤል ተ/ሚካኤል ወደ ግብነት ቀይሮ ቡናማዎቹን ወደ ጨዋታ መልሷል።

በተቃራኒዉ በ73ኛዉ ደቂቃ ላይ ከማዕዘን የተሻገረዉን ኳስ የቡና ተከላካዮች ለመከላከል በሚጥሩበት ወቅት ኳሷ ተጨራርፋ ወደ ራሳቸዉ ግብ ብትቆጠርም ጥፋት ተሰርቷል በሚል ጎሉ ተሽሯል።

መደበኛዉ የጨዋታ ደቂቃ ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቀማዎች ሲቀሩት ግን ባህርዳር ከተማዎች ሶስተኛ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም በ88ኛዉ ደቂቃ ላይ ርቤል ተ/ሚካኤል ፋሲል አስማማዉ ላይ የሰራዉን ጥፋት ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት አምበሉ ያሬድ ባየ ወደ ግብነት ቀይሮ የጣና ሞገዶቹን የግብ መጠን ወደ ሶስት ከፍ ማድረግ ችሎ ጨዋታዉም በባህርዳር ከተማ 3ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

” አምናና ካቻምና ገጥሞን እንደነበረው የፋይናንስ ክፍተት ዘንድሮ ግን አንቸገርም” አቶ ዳዊት ውብሸት / የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፖርት ማህበር የቦርድ አባል/

የሱፐር ስፖርት የቀጥታ ስርጭት ለምን ተቋረጠ … ?

የአመቱ ኮከብ ተመራጮች የሽልማት ገንዘብ አለመከፈሉ አነጋጋሪ ሆኗል

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የመቻል ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ረቷል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣዜናዎች

ሀትሪክ ተመለሰች ረቡዕ ማለዳ በገበያ ላይ ትውላለች!

hatricksport team By hatricksport team 4 years ago
በዝውውር መስኮቱ 17 ተጨዋቾች ብቻ ዝውውራቸው ጸድቋል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ጅማ አባ ጅፋር | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ ቡና በአቡበከር ናስር ሁለት ግቦች ታግዞ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል
ውጤት ለእኛ በቂ አይደለም” ይገዙ ቦጋለ /ሲዳማ ቡና/
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?