መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ረቷል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮ-ኤሌክትሪክዜናዎችየጨዋታ ዘገባድሬዳዋ ከተማ

የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ረቷል

አጋራ
አጋራ

በሊጉ የስምንተኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ሁለተኛ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 አሸንፏል ።

ድሬዳዋ ከተማዎች በሰባተኛው ሳምንት ከመቻል አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አንድ ለውጥ ብቻ ያደረጉ ሲሆን ብሩክ ቃልቦሬን በአቤል አሰበ ምትክ አሰልፈዋል ። በአንፃሩ ኢትዮ ኤሌክትሪኮች በሳምንቱ በኢትዮጵያ መድኅን በተረቱበት ጨዋታ ላይ ከነበረው ምርጥ አስራአንድ ሁለት ቅያሪዎችን በማድረግ በአላዛር ሽመልስ እና ኢብራሂም ከድር ምትክ ማታይ ሉል እና ልደቱ ለማ ጨዋታውን እንዲጀምሩ ማድረግ ችለዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም ቡድኖች በኩል ጨዋታውኝ ለመቆጣጠር ጥረቶችን ያደረጉበት ነበር ።

በዚህም የተሻሉ የነበሩት ኢትዮ ኤሌክትሪኮች በዘጠነኛው ደቂቃ ላይ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ አግኝተዋል ። የድሬዳዋ ከተማን የኳስ ምስረታ በማቋረጥ ያገኘውን አጋጣሚ በመጠቀም ናትናኤል ሰለሞን ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

ከግቡ መቆጠር በኋላ ድሬዳዋ ከተማዎች የአቻነት ግብ ለማግኘት ተጭነው ለመጫወት ጥረቶችን አድርገዋል ። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ተጫዋቾች ግን የድሬዳዋ ከተማን የማጥቃት ሂደት የተሳለጠ እንዲሆን የፈቀዱ አልነበሩም ።

ይህንን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማዎች ረጃጅም ኳሶችን ወደ ፊት በመጣልም ዕድሎችን ለመፍጠር ሲሞክሩ ተስተውሏል ።

ከግብ ሙከራ የራቀው የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያው ላይ ምናልባትም የኢትዮ ኤሌክትሪክን የግብ መጠን ወደ ሁለት ከፍ ሊያደርግ የሚችል አጋጣሚን አስመልክቶናል ። አጥቂው ልደቱ ለማ የድሬዳዋ ከተማ ተከላካይ የሆነውይ የአሳንቴ ጎድፍሬድን ስህትት ተጠቅሞ ወደ ግብ የመታው ኳስ በዳንኤል ተሾመ ግብ ከመሆን ድኗል ።

የመጀመሪያው አጋማሽም በኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪነት ተጠናቀቀ ።

በሁለተኛው አጋማሽ የመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጫና ፈጥረው በመጫወት ወደ ድሬዳዋ ከተማ የግብ ክልል ለመድረስ ችለው ነበር ።

በዚህም በ49ኛው ደቂቃ ላይ ስንታየሁ ወለጬ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ገብቶ ወደ ግብ ያደረገው ጠንካራ የግብ ሙከራ በዳንኤል ተሾመ ተመልሷል ።

ድሬዳዋ ከተማዎች በመልሶ ማጥቃት እንቅስቃሴ ወደ ተጋጣሚያቸው የግብ ክልል ለማድረስ ጥረቶችን በማድረግ የጀመሩት የጨዋታ ሂደት ቀስ በቀስ በማሻሻል ከተጋጣሚያቸው የተሻለ እንቅስቃሴ ማድረግ ችለዋል ።

ነገር ግን የግብ ዕድል ለመፍጠር እስከ 66ኛው ደቂቄ ለመጠበቅ ተገደው ነበር ። በተጠቀሰው ደቂቃ ላይ መሀመድ አብዱለጢፍ ከቅጣት ምት ያሻገረውን ኳስ አሳንቴ ጎድፍሬድ በግንባር ገጭቶ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል ።

ድሬዳዋ ከተማዎች በአመዛኙ በግራ መስመር በኩል ጫና ሲፈጥሩ ቆይተው በ74ኛው ደቂቃ ከዚሁ አቅጣጫ በተነሳ ኳስ የኢትዮ ኤሌክትሪክን መረብ ማግኘት ችለዋል ። ሙኸዲን ሙሳ በግራ መስመር ይዞ ወደ ሳጥን የገባውን ኳስ አሻምቶ ቢንያም ጌታቸው በግንባር በመግጨት ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

ከአቻነቱ ግብ በኋላ የተነቃቁት ድሬዳዋ ከተማዎች በ88ኛው ደቂቃ ላይ ከመመራት ወደ መምራት የተሸጋገሩበትን ግብ አስቆጥረዋል ። ቻርለስ ሙሴጌ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ተከላካዮች መዘናጋትን ተከትሎ ያገኘውን ኳስ ወደ ሳጥን ይዞ በመግባት በዘሪሁን መረብ ላይ አሳርፏል ።

በመጨረሻም ድሬዳዋ ከተማ በ2 ለ 1 ድል ከጨዋታው ሙሉ ሶስት ነጥብ ይዘው መውጣት ችለዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...