መነሻ ገጽ መቻል የጨዋታ ዘገባ | የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የመቻል ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል
መቻልቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የመቻል ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል

አጋራ
አጋራ

ምሽት ላይ የተደረገው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የመቻል ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል ።

ቅዱስ ጊዮርጊሶች በሰባተኛው ሳምንት ከወልቂጤ ከተማ አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አንድ ለውጥ በማድረግ የገቡ ሲሆን ባህሩ ነጋሽን በቻርለሽ ሉክዋጎ ምትክ ተክተቃል ። በመቻል በኩል ደግሞ በስድስተኛው ሳምንተሰ በወላይታ ድቻ በተረተቡት ጨዋታ ላይ ከነበረው ምርጥ አስራ አንድ ሁለት ቅያሪዎችን በማድረግ በግርማ ዲሳሳ እና ከነአን ማርክነህ ምትክ ፍፁም አለሙን እና በረከት ደሰታን አሰልፈዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል የመድረስ ጥረቶች ቢታዩም ቀስ በቀስ ፈረሰኞቹ በኳስ ቁጥጥሩ የተሻሉ ሆነው ታይተዋል ።

ምንም እንኳን ቅዱስ ጊዮርጊሶች የኳስ ቁጥጥር የበላይነት ቢወስዱም ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመድረሱ ረገድ ደካማ ነበሩ ። በአንፃሩ በመቻል በኩል የተጋጣሚን የኳስ ፍሰት በማቋረጥ የሚገኙ ኳሶችን በፈጣን እንቅስቃሴ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ የግብ ክልል በማድረስ በተሻለ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ችለዋል ።

በነዚህ ደቂቃዎች ላይ መቻሎች በግሩም ሀጎስ እና ከነአን ማርክነህ አማካኝነት ያደረጓቸው የግብ ሙከራዎች ኳሶቹ ኢላማዎች ባለመጠበቃቸው ውጤታማ ሳይሆኑ ቀርተዋል ።

በ18ኛው ደቂቃ ላይ ፈረሰኞቹ ቀዳሚ የግብ ሙከራቸውን አድርገዋል ። ሄኖክ አዱኛ ከማዕዘን ያሻገረውን ኳስ ቸርነት ጉግሳ በግንባር ገጭቶ ወደ ግብ ልኮት የነበረ ቢሆንም የመቻሉ ግብ ጠባቂ ዳግም ተፈራ ግብ ከመሆን አድኖታል ።

ጨዋታው በተመሳሳይ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ቀጥሎ ሻምፕየኖቹ መሪ መሆን የሚችሉበትን ዕድል 42ኛው ደቂቃ ላይ አስመልክቶናል ። አማኑኤል ገብረሚካኤል ከቢንያም በላይ ጋር በአንድ ሁለት ቅብበል ወደ ሳጥን ይዞ የገባውን ኳስ ነው ሳይጠቀምበት የቀረው ።

በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ፈረሰኞቹ በኳስ ቁጥጥሩ የበላይነታቸው ቀጥለው የነበረ ቢሆንም የማጥቃት ሶስተኛው ዞን ላይ የነበራቸው ደካማ እንቅስቃሴ ጥረቶቻቸው በግብም ሆነ በግብ ሙከራ እንዳይታጀቡ አድርጓቸዋል ።

በመቻል በኩል የመልሶ ማጥቃት ዕድሎችን የመጠቀም የመጀመሪያ አጋማሽ ፍላጎት በሁለተኛው አጋማሽም ቀጥሎ የነበረ ቢሆንም ባሆሩ ነጋሽን የፈተኑ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ተቸግረው ቆይተዋል ።

በ49ኛው ደቂቃ ላይ ቅዱስ ጊዮርጊሶች ያገኙትን የቅጣት ምት ሱሌማን ሀሚድ ወደ ተጋጣሚ ሳጥን አሻግሮ ከነአን ማርክነህ ኳሱን ለማውጣት ሲሞክር ለጥቂት ራሱ ላይ አስቆጥሮ ነበር ።

መቻሎች በቀጣይ አከታትለው ሁለት የግብ ሙከራዎችን ያደረጉ ሲሆን ኢላማቸውን ግን የጠበቁ አልነበሩም ።

ቀዳሚው የሳሙኤል ሳሊሶ ሲሆን በ59ኛው ደቂቃ ላይ ከማዕዘን ተሻምቶ በግብ ጠባቂው የተመለሰውነሰ ኳስ ከሳጥን ውጪ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ ሳይሳካለት ቀርቷል ። በ70ኛው ደቂቃ ላይም በረከት ደስታም በበኩሉ በሳጥኑ የግራ አቅጣጫ ይዞ የገባውን ኳስ ወደ ግብ መሞከር ቢችልም ባህሩን የፈተነ አልበረም ።


በ74ኛው ደቂቃ ላይ በፈረሰኞቹ በኩል ከቅጣት ምት ወደ ግብ የተሻገረውን ኳስ የመቻል ተጫዋቾች በአግባቡ ከግብ ክልል ሳያርቁ በመቅረታቸው አቤች ያለው አግኝቶ ወደ ግብ የሞከረው ኳስ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል ።

በመጨረሻም ጨዋታው ግብ ሳያስተናግድ በአቻ ውጤት ተጠናቋል ።

በሊጉ የዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ህዳር 13(ማክሰኞ) ቀን 10:00 ላይ መቻል ሲዳማ ቡናን ሲገጥም በዕለቱ ምሸት 1:00 ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀዋሳ ከተማ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...