አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱን ከቀጠሩ በኋላ የተለያዩ አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ በመቀላቀል ላይ የሚገኙት የጣና ሞገዶቹ አሁን ደግሞ ከሁለቱ ተጫዋቾቻቸው ወሰኑ አሊ እና ሚኪያስ ግርማ ጋር በስምምነት መለያየታቸው ዕርግጥ ሆኖአል።
የቀድሞው የኢትዮጵያ መድን ተጫዋች የነበረዉ የመስመር አጥቂዉ ወሰኑ አሊ ባህር ዳር ከተማ ከከፍተኛ ሊጉ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሲያድግ የስብስቡ አባል እንደነበረ ይታወቃል። ከ2011 የዉድድር አመት አንስቶ ከባህርዳር ከተማ ጋር በፕሪምየር ሊጉ መቆየት የቻለዉ ተጫዋቹ ከአራት አመታት ቆይታ በኋላ ከክለቡ ጋር በስምምነት መለያየቱ ተረጋግጧል።
ሌላኛው ከክለቡ ጋር የተለያየዉ ደግሞ የቀኝ መስመር ተከላካዩ ሚኪያስ ግርማ መሆኑ ታዉቋል ። የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ ፤ አራዳ ክ/ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ተጫዋች የነበረዉ ተከላካዩ እንደ ክለብ አጋሩ ወሰኑ አሊ ሁሉ እርሱም ከ አራት አመታት የባህርዳር ቆይታ በኋላ ከጣና ሞገዶቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል ። ተጫዋቾች ከባህርዳር ከተማ ጋር በስምምነት መለያየታቸውን ተከተሎ በቀጣይ ቀናቶች ወደ ሌሎች ክለቦች ያመራሉ ተብሎ ይጠበቃል።