ዘንድሮ በሊጉ ዝቅተኛ ነጥብን በመሰብሰብ ወርደዉ የነበሩት ጅማዎች ዳግም ያገኙትን ዕድል ተጠቅመው ወደ ሊጉ መመለሳቸው ይታወሳል። ይሄንንም ተከትሎ በቀጣዩ አመት ጥሩ ተፎካካሪ ሆነዉ ለመቅረብ ከወዲሁ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ በመቀላቀል ላይ ይገኛሉ በዛሬዉ ዕለት ደግሞ ከእያሱ ለገሰ በመቀጠል የሁለት ተጫዋቾችን ዝዉዉር አጠናቀዋል።
የዉድድር አመቱን በወልቂጤ ከተማ ያሳለፈው ተስፋዬ መላኩ በአሸናፊ በቀለ ወደ የሚሰለጥነው ጅማ አባጅፋር ያመራ ቀዳሚዉ ተጫዋች ነዉ።
ሌላኛው ክለቡን የተቀላቀለዉ ደግሞ ግብ ጠባቂው ዮሀንስ በዛብህ መሆኑ ዕርግጥ ሆኖአል። እንደ ቡድን አጋሩ ተስፋየ ዉድድር አመቱን በወልቂጤ ያሳለፈዉ የግብ ዘቡ ከክትፎዎቹ ቤት በመልቀቅ ወደ ጅማ አባጅፋር ማምራቱ ታዉቋል።
አስተያየት ይስጡ