አትሌት ትዕግስት አሰፋ የ2023 የበርሊን ማራቶን 2:11:53 በመግባት የዓለም የሴቶች የማራቶን ክብረወሰንን በመስበር ጭምር አሸንፋለች ።
አትሌቷ ያሻሻለችው ክብረወሰን ቀደም ብሎ ተመዝግቦ ከነበረው ሰዓት ከሁለት ደቂቃዎች በላይ ባነሰ ጊዜ ነው ።
ቀደም ብሎ የነበረው የርቀቱ ክብረወሰን በ2019 በኬንያዊቷ ብሪጂድ ኮስጌይ 2:14:04 የመዘገበ ነበር ።
አትሌት ትዕግሰት በ2022 የበርሊን ማራቶንም በ2:15:37 በመግባት በቀዳሚነት ማጠናቀቋ ይታወሳል ።