በ17ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ቀን 7:00 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ኢትዮጵያ መድንን በመለያ ምት 5ለ3 በሆነ ዉጤት በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆን ሲችል ፤ በሁለተኛዉ የግማሽ ፍፃሜ ተጠባቂ ጨዋታም ቀን 9:00 ሰዓት ላይ በሸገር ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና ቅ/ጊዮርጊስን በመለያ ምት 5ለ4 በሆነ ዉጤት በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆን ችሏል።
በዚህም ተጠባቂ በነበረዉ የቀን 9:00 ሰዓቱ ጨዋታ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሀሮን አንተር የ13ኛ ደቂቃ ጎል መሪ መሆን ችሎ የነበረ ሲሆን ወልደአማኑኤል ጌቱ በ26ኛው ደቂቃ ላይ ለቡናማዎቹ የአቻነት ግብ አስቆጥሮ በመደበኛዉ ዘጠና ደቂቃ አንድ አቻ በሆነ ዉጤት ፍፃሜዉን አጊኝቷል ፤ ይህንንም ተከትሎ በተሰጠዉ የመለያ ምት ቡናማዎቹ 5ለ4 በሆነ ዉጤት በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆን ችለዋል።
- ማሰታውቂያ -
በጨዋታውም ኮከብ ተብሎ የተመረጠዉ የኢትዮጵያ ቡናው በፍቃዱ አለማየሁ ከእለቱ የክብር እንግዳ ከአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ም/ቢሮ ሀላፊ ከአቶ ተስፋየ ኦሜጋ እጅ ሽልማቱን ተረክቧል። የዛሬዉን ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዉጤት ተከትሎም የፊታችን ሀሙስ ኢትዮጵያ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና ለዋንጫ ሲጫወቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ መድንም ለደረጃ የሚጫወቱ ይሆናሉ።