ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እና በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተለያዩ ክለቦች ዉስጥ በብቃት ለረዥም አመታት መጫወት የቻለዉ የቀድሞዉ የወላይታ ዲቻ ተጫዋች ደጉ ደበበ በአርባምንጭ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ዉስጥ በሁለት ሀላፊነቶች ተሹሟል።
በዚህም መሰረት የአርባምንጭ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ባደረገዉ አስቸኳይ ስብሰባ ደጉ ደበበን የአርባምንጭ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ቴክኒካል አማካሪ እና የክለቡ የቡድን መሪ አድርጎ ሾሟል።