ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ከጥር 1/2014 ዓ.ም በካሜሩን በተጀመረው የ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ኢትዮጵያን ከወከሉ ባለሙያዎች መካከል አንዱ እንደሆነ ይታወቃል።
ከባምላክ ተሰማ በተጨማሪ ኢትዮጵያዊው ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ በአፍሪካ ዋንጫዉ ቴክኒክ ክፍሉ እየሰሩ ሲሆን ከቀናት በፊት ሴኔጋል ወደ ግማሽ ፍፃሜው ስታልፍ ኢኳቶሪያል ጊኒን 3 ለ 1 ባሸነፈችበት ጨዋታ በቴክኒክ ክፍል ውስጥ እንደተሳተፉ ይታወሳል።
ዛሬ ደግሞ ለዋንጫ ለማለፍ ሴኔጋል ከቡርኪናፋሶ የሚያደርጉትን ጨዋታ ኢትዮዽያዊው የመሀል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ከረዳቶቻቸዉ ሱዳናዊዩ ኢብራሂም አብደላ እና ኬንያዊዩ ጊልበርት ቸሪዮት እንዲሁም ሊቢያዊዩ ፒተር ካማኩ ጋር በመሆን ጨዋታዉን የሚመሩ ይሆናል።
ተጠባቂዉ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታም በቡርኪናፋሶ እና ሴኔጋል መካከል ምሽት 04:00 ሰዓት ላይ የሚደረግ ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ