በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመጀመሪያ የዙር ጨዋታ ከሜማሎ ሰንዳውንስ ጋር ነጥብ ተጋርቶ ወጧል
በቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያ አሰላለፍ 4-2-3-1 በአደነ ግርማ የፊት አጥቂነት ሲጀምር
በሰንዳውንስ በኩል በተመሳሳይ በ 4-2-3-1 አሰላለፍ ጨዋታቸውን ጀምረዋል
- ማሰታውቂያ -
ጨወታው እንደተጀመረ የጨዋታ ብልጫውን መውሰድ የቻሉት ሰንዳውንሶች ሲሆኑ በ5 ኛ እና በ8ኛ ደቂቃ ላይ አስደንጋጭ ሙከራዎች አድረገው በሮበርቶ ኦዶንኳራ አስደናቂ ብቃት ጎል ከመሆን ድንዋል፡፡
በጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ግዜ ሙሉ ለ የጨዋታ ብልጫ ሰንዳውንሶች ሲወስዱ በፈረሰኞቹ በኩል ሙሉ በሙሉ የመከላከል ሚና ውስጥ ገብተው ተይተዋል ይህም ለሰንዳውሰኖች ነፃ ሆነው እንዲጫወቱ አድል ፈጥሮላቸዋል ፡፡
በፈረሰኞቹ በኩል በ30 እና በ36 ደቂቃ አደነ ግርማ ከመሀል ሜዳ አለፍ ብሎ አክርሮ የመታውኳስ በግብ ጠባቂው ሲመለስ; ተስፋዬ አለባቸው ከርቀት አክርሮ የመታው ኳስ በጎሉ አናት ላይ ወጧል፡፡በዚሁ መጀመሪያው አጋማሽ ሲጠናቀቅ
በሁለተኛው የጨዋታው አጋማሽ በቅዱስ ጊዮርጊስ አማካኝነት ጨዋታው ሲጀመር
በ46ኛ ደቂቃ ራምኬሎ በጥፊ ተመትቶ መሃል ሜዳ ላይ ሲወድቅ ዳኛው የሰንዳወንሱን ተጨዋቾች ያለምንም ማስጠንቀቂያ ካርድ አልፈዋል ፡፡
ጨዋታው በቀጠለ በ52ኛ ደቂቃ ደጉ ደበበ ከመስመር የተሻገረውን ኳስ በግሩም ሁኔታ ማውጣት ችልዋል፡፡63ኛ ደቂቃ ላይ የተጫዋች ቅያሪ ሲያደርጉ ፕሪንስ አስወጥተው ምንያህል ተሾመን ወደሜዳ አስገብተዋል፡፡
በሁለተኛው የጨዋታ አጋማሽ ፍጥነት የበዛበትና ቶሎ ቶሎ ወደ ጎል ሁለቱም ቡድኖች ሲደርሱ በ73′ ደቂቃ አስቻለው ታመነ አደገኛ ቦታ ላይ በሰራው ጥፋት ቅጣት ምት ያገኙት ሰንዳውሰኖች በሮበርቶ ኦዶንኮራ ግሩም ብቃት ከሽፎባቸዋል፡፡
ጨዋታው ሊጠናቀቅ 10 ደቂቃዎች ሲቀሩት ሁለተኛ የተጫዋች ቅያሪ ያደርጉት ፈረሰኞቹ ተስፋዬ አለባቸውን በያሲር ሙጌርዋ ቀይረዋል፡፡
በጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ ጫና መፍጠር የቻሉት ሰንዳውንሶች አስቻለው በሰራው ጥፋት ያገኙትን እድል ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል በ90ኛ ደቂቃ የሰንዳውንሱ ቱዋ አደገኛ ኳስ የጊዮርጊስ የግብ ክልል ይዞ ሲገባ ናትናኤል ኳሱን ተደርቦ በመከለል የመልስ ምት እንድቶን አድርጓታል፡፡ጨወታው ተጠናቆ በ93ኛ ደቂቃ ላይ ፈረሰኞቹ የመጨረሻ ሶስተኛ ቅያሪያቸውን ሲያደርጉ አዳነ ግርማን በአቡበከር ቀይረዋል፡፡ የጨዋታውን መጠናቀቅ በ94ኛ ደቂቃ ላይ ግብፃዊው አልቢተር የጨዋታውን መጠናቀቅ አብሰረው ጨዋታው ተጠናቋል ፡፡
በሳውዝ አፍሪካ እሚገኙ ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ወክሎ ለሚፋለመው ቅዱስ ጊዮርጊስ ያሳዩት ድጋፍ አስደናቂ እንደነበር ለመታዘብ ችለናል፡፡በዚህም የሀትሪክ ስፖርት ድህረ-ገፅ በሳውዝ አፍሪካ እሚገኙ ኢትዮጵያንን ሳታመሰግን አታልፍም፡፡