መነሻ ገጽ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከተማ ሸገር ላይ ድል ቀንቶታል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ፋሲል ከተማ ሸገር ላይ ድል ቀንቶታል

አጋራ
አጋራ

20ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር አንድ ጨዋታ ዛሬ ተደርጓል።

በአዲስ አበባ ስታዲየም ፋሲል ከተማ ከወልድያ 9 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን አድርገዋል።

በሁለተኛው ዙር የሊጉ መርሃ ግብር ነጥብ መያዝ የተሳነው ፋሲል ከተማ፥ በይስሃቅ መኩሪያ ብቸኛ ጎል ሶስት ነጥብ ይዞ መውጣት ችሏል።

17523538_1839936212933285_151695390110997350_n

 

ውጤቱን ተከትሎም ፋሲል ከተማ በ19 ጨዋታ 29 ነጥብ መያዝ ችሏል።17523390_1839930926267147_4419156589029545440_n

ፋሲል ጎንደር ላይ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ሲጫዎት በተፈጠረ የደጋፊ ረብሻ ምክንያት፥ አንድ ጨዋታ ከሜዳው ውጭ እንዲጫዎት በመወሰኑ ምክንያት ነበር የዛሬውን ጨዋታ አዲስ አበባ ላይ ያደረገው።

17554570_1839953622931544_1040245853782904026_n

ሌሎች ጨዋታዎች ነገ ቀጥለው ሲካሄዱ አዲስ አበባ ላይ መከላከያ ከሃዋሳ ከተማ ይገናኛሉ።

አርባ ምንጭ ላይ ደግሞ አርባ ምንጭ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ እንዲሁም አዳማ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ አዳማ ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ሁሉም ጨዋታዎች በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ይሆናል።

ከነገ በስቲያ ሃሙስ ደግሞ በሃዋሳ ስታዲየም በቡና ደርቢ፥ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ቡና ይጫወታሉ።

ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ19 ጨዋታዎች 35 ነጥብ ይዞ ሲመራ፥ ደደቢት በ20 ጨዋታዎች በተመሳሳይ ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ ይከተላል።

ሲዳማ ቡና በ19 ጨዋታ 33 ነጥብ እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና በተመሳሳይ ጨዋታ 32 ነጥቦች በመያዝ ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አዲስ አበባ ከተማ በ20 ጨዋታ በተመሳሳይ 15 ነጥቦች የደረጃውን ግርጌ ይዘዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...