መነሻ ገጽ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ ሁለተኛውን ተጫዋች አስፈረመ
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግድሬዳዋ ከተማ

ድሬዳዋ ከተማ ሁለተኛውን ተጫዋች አስፈረመ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊው ክለብ ድሬዳዋ ከተማ በእግር ኳስ ተጨዋችነት ጉዞው ለሙገር ሲሚንቶ፣ ለአዲስ አበባ ከተማ፣ ለጅማ አባቡና፣ ለአዳማ ከተማ እና ለሀድያ ሆሳህና በአጥቂ አማካይ ስፍራ የተጫወተውን ሱራፌል ጌታቸውን በማስፈረም የክለቡ ንብረት አድርጎታል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ በርካታ ተጨዋቾችን ኮትኩቶ በማሳደግ ከሚታወቀው ሙገር ሲሚንቶ በመገኘት እስከ ኢትዮጵያ ታዳጊ ወጣት እና የኦሎምፒክ ቡድን ለመመረጥ የቻለው ይኸው ተደናቂ ወጣት ተጨዋች ጥሩ ብቃቱን በማሳየት የሚታወቅ ሲሆን ሀድያ ሆሳህና ፕሪምየር ሊጉን እንዲቀላቀልም ትልቁን አስተዋፅኦ ከማበርከቱ በተጨማሪ የከፍተኛ ሊጉ የኮከብ ተጨዋች ምርጫ እጩዎቹ ውስጥም ገብቶ እንደነበር ይታወሳል።
ድሬዳዋ ከተማ ሱራፌልን ያስፈረመው ለአንድ አመት ውል ሲሆን ተጨዋቹ በብርቱካናማዎቹ ማሊያ ጥሩ ጊዜን ያሳልፋል ተብሎም ተጠብቋል።

ድሬዳዋ ከተማ ሱራፌልን ሲያስፈርም ሁለተኛው የክለቡ ተጨዋች ሲሆን ከሐዋሳ ከተማ የመጣው አስጨናቂ ሉቃስ የመጀመሪያው ፈራሚም ሆኗል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...