መነሻ ገጽ አርባምንጭ ከተማ የጨዋታ ዳሰሳ | አርባምንጭከተማ ከ ውልዋሎ ዓዲግራት.ዩ
አርባምንጭ ከተማወልዋሎየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዳሰሳ

የጨዋታ ዳሰሳ | አርባምንጭከተማ ከ ውልዋሎ ዓዲግራት.ዩ

አጋራ
አጋራ

በ6 ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መርሀግብር ቅዳሜ አና እሁድ በሚደረጉ ጨዋታወች ቀጥሎ ሲውል እሁድ ታህሳስ1 ከሚደረጉ የክልል ጨዋታዎች መካከል አርባምንጭ ላይ አርባምንጭከተማ የሊጉን መሪ አዲስ አዳጊውን ውልዋሎ ዓዲግራት.ዩ ሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ በዚህ ጨዋታ ላይ አንዳንድ ነጥቦች እናያለን፡፡
የመጀመሪያውን 4 ጨዋታወች በውጤት ቀውስ ውስጥ የነበረው አርባምንጭ ከተማ በ5 ሳምንት መርሀግብር መከላከያን በሜዳው በታዳግው አጥቂ ብርሀኑ አዳሙ ና በተከላካዩ ፀጋዬ አበራ ሁለት ግቦች 2-0 በማሸነፍ በጥቂቱ እፎይታን ቢያገኙም የነገውን ጨዋታ በማሸነፍ ሙሉ ለሙሉ ከወራጅ ቀጠናው በመውጣት ወደ ዋንጫው ፉክክር ግስጋሴ ለመቀላቀል እንደሚጫወት ይጠበቃል፡፡
በአንፃሩ ውልዋሎ ከመጀመሪያው ሳምንታት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ቢጀምርም ቡድኑ ያለበትን ክፍተት በማስተካከል በ4 ሳምንት አዲስአበባ ላይ ኢትዮ-ኤሌክትሪክን 3-1 አንዲሁም በ5 ሳምንት ዓዲግራት ላይ ኢትዮጵያ ቡናን 1-0 በማሸነፉ በ9 ነጥብ የሊጉ መሪ መሆን ችሏል፡፡ 
የአሰልጣኝ ብርሀኔ ስብስብ ኳስን መሰረት አድርጎ የሚጫወቱ ተጫዋቾችን የያዘ ብድን ስሆን፡፡ በነገውን ጨዋታ በሁለቱም ቡድኖች በኩል ኳስን መሠረት ያደረገ የጨዋታ ስልት እደሚተገብሩ ይጠበቃል፡፡

የፀጋዬ ኪዳነማርያሙ አርባምንጭ ከተማ መከላከያ ላይ ይዞት የገባውን የ3-5-2 አዲስ አሰላለፍ ይዞ ወደ ሜዳ የሚገባ ስሆን፡፡
ውልዋሎ በአነፃሩ 4-5-1 በሆነ የመልሶ ማጥቃት አሰላለፍ በመጠቀም ውጤት ይዞ ለመወጣት ወደ ሜዳ እደሚገባ ይጠበቃል፡፡

ተከላካዩን ተመስገን ካስትሮን ና አማካኙን እንዳለ ከበደን ለብሔራዊ ብድን ያስመረጠው አርባምንጭከተማ አንድነት አዳነ (ማንጋላ) በቅጣት አንበሉን አማኑኤል ጎበና ና አጥቂውን ተሾመ ታደሰ(ክሮች) በጉዳት የሚያጣ ስሆን፡፡ 
በውልዋሎ በኩል ግብ ጠባቂው በረከት ለብሔራዊ ብድን በመመረጡ እማይኖር ሲሆን ቡሩክ አየለ እና እዮብ ወልደማርያም በጉዳት ምክኒያት ወደ አርባምንጭ ሳይጓዙ መቀረታቸው ሲሰማ፤
ከኢትዮጵያ ቡና ጋር በነበረው ጨዋታ መጠነኛ ጉዳት ያጋጠመው በረኛው ዘውድ መስፍንም ከነጉዳቱ ይሰለፋል ተብሎ ይጠበቃል

በዛሬው እለት ሁለቱም ብድኖች የመጨረሻ ልምምዳቸውን በማድረግ ለነገው ጨዋታ ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...