መነሻ ገጽ ኢትዮጵያ ቡና የጨዋታ ቅድመ ዳሰሳ | ኢትዮጵያ ቡና ከሀድያ ሆሳዕና
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዳሰሳ

የጨዋታ ቅድመ ዳሰሳ | ኢትዮጵያ ቡና ከሀድያ ሆሳዕና

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር እንዲህ እንዲያ እያለ እነሆ 6ኛ ሳምንት ላይ ደርሷል። ሊጉ እስካሁን ድረስም ለ5 ሳምንታት በፍጹም ስፖርታዊ ጨዋነት እና እንግዳ ክለብን በመልካም አቀባበል እየተካሄደ ሲሆን ይህም ይበል የሚያስብል ሆኖ እስከ ሊጉ ፍፃሜ መቀጠል አለበት ብለን እናምናለን።

በሊጉ 6ኛ ሳምንት 8ጨዋታዎች በሳምንቱ መጨረሻ የሚካሄዱ ሲሆን አርብ እና እሁድ አንድ አንድ እንዲሁም ቅዳሜ ስድስት ጨዋታዎች የሚደረጉ ይሆናል። ከሚደረጉት ጨዋታዎች መካከል 5ቱ ጨዋታዎች ክልል ላይ ሲደረጉ ቀሪዎቹ 3ጨዋታዎች ደግሞ አዲስ አበባ ላይ የሚደረጉ ይሆናል። ከነዚህ ጨዋታዎች መካከል ነገ(ቅዳሜ) አዲስ አበባ ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከሀድያ ሆሳዕና የሚያደርጉትን ጨዋታ በዚህ ቅድመ ዳሰሳ ለእናንተ እንዲስማማ አድርገን አቅርበንላችኋል። መልካም ንባብ።

ጨዋታ: ኢትዮጵያ ቡና ከሀድያ ሆሳዕና
የጨዋታ ቀን: ቅዳሜ ታህሳስ 25/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር: ፌደራል አርቢትር ዮናስ ካሳሁን
የጨዋታ ቦታ: አዲስ አበባ ስታዲየም

በብዙ ደጋፊዎች ውብ ዝማሬ ፊት እንደሚካሄድ የሚጠበቀው ይህ ጨዋታ በፌደራል አርቢትር ዮናስ ካሳሁን መሪነት ቅዳሜ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

ኢትዮጵያ ቡናዎች በካሳዬ አራጌ እተመሩ በሜዳ ላይ እንቅሰቃሴ ከጨዋታ ጨዋታ የተሻለ ነገሮችን ማሳየታቸውን ቢቀጥሉም አሁንም ግን ከሜዳቸው ውጪ ማሸነፈ ተስኗቸው ታይቷል። በሊጉ አምስተኛ ሳምንት መርሀ ግብር ከድሬድዋ ጋር አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ሲሆን በዕለተ ቅዳሜ በሚካሄደው መርሀ ግብር አዲስ አዳጊውን እና በውጤት ቀውስ ውስጥ የሚገኘውን ሀድያ ሆሳዕናን በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚያስተናግዱ ይሆናል።

ሀድያ ሆሳዕና በአምስተኛው የሊጉ ሳምንት በፊት መስመሩ ከጨዋታ ጨዋታ ጥሩ ጥምረትን እና አስፈሪ እየሆነ የመጣውን ባህርዳር ከተማን በሜዳቸው አስተናግደው ሁለቴ ከመመራት ተነስተው አቻ ውጤት ማስመዝገባቸው አይረሴ ነው ፡፡ ሀድያ ሆሳዕና በሁለት ነጥብ እና በአምስት የግብ እዳ የሊጉ ግረጌ ላይ ሲገኝ በጨዋታው ድል የሚቀናው ከሆነ የሌሎች ቡድኖች ነጥብ መጣልን ጠብቆ እስከ አስራ ሶስተኛ ደረጃ ከፍ የማለት ተስፋን ሰንቆ ወደ ሜዳ የሚገቡ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...