በ19ኛው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ዛሬ በተካሄደው የእግር ኳስ ጨዋታ ወላይታ ድቻና ሲዳማ ቡና አቻ ዜሮ ለዜሮ ተለያዩ፡፡
በመጀመሪያዉ የጨዋታ ክፍሌ ጊዜ ኳስ በማደራጀት፣ በመከላከልና የመሃል ሜዳዉን በመቆጣጠር የሲዳማ ቡና ቡድን ሲበልጥ ወደ ጎል በመድረስና አጋጣሚዎችን በመፍጠር ድቻ የተሻለ ነበር፡፡
በሁለተኛዉ የጨዋታ ክፍሌ ጊዜ የወላይታ ድቻ ቡድን ራሱን አደራጅቶ በመግባት በመከላከል፣ በማደራጀትና በማጥቃቱም የተሻለ ብልጫ የነበረው ቢሆንም ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡
የወላይታ ድቻ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ “ከሽንፈት የተመለስን በመሆናችን አንድ ነጥብ ማግኘታችን የሚያስከፋ ባይሆንም የፈጠርናቸው የጎል አጋጣሚዎች መጠቀም አለመቻላችንና በሜዳችን ሙሉ ነጥብ ያለመውሰዳችን ያስቆጫል” ብለዋል፡፡

በአጨራረስ ክፍተት እያስከፈላቸውን ያለውን ዋጋ ለመመለስ ተኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

የሲዳማ ቡና አሰልጣኝ አለማየሁ አባይነህ (አለኮ) ” በመጀመሪያው የጨዋታ ከፍለ ጊዜ መጨረስ ሲገባን ያገኘናቸውን አጋጣሚዎች መጠቀም ያለመቻላችን ነጥብ እንድንጥል አድርጎናል” ብለዋል፡፡
ከሜዳቸው ውጭ ተጫውተው አንድ ነጥብ ማግኘታቸው መልካም መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ዳኝነቱም የተሻለ መሆኑን ጠቁመዉ በሜዳዉ የተመለከቱት የስፖርታዊ ጨዋነት የተላበሰ የድጋፍ አሰጣጥ መቀጠል እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት ይስጡ