መነሻ ገጽ Uncategorized የጨዋታ ሪፖርት:ወላይታ ድቻና ሲዳማ ቡና አቻ ተለያዩ
Uncategorizedየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ሪፖርት:ወላይታ ድቻና ሲዳማ ቡና አቻ ተለያዩ

አጋራ
አጋራ

በ19ኛው  የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ዛሬ  በተካሄደው የእግር ኳስ ጨዋታ ወላይታ ድቻና ሲዳማ ቡና አቻ ዜሮ ለዜሮ ተለያዩ፡፡

በመጀመሪያዉ የጨዋታ ክፍሌ ጊዜ ኳስ  በማደራጀት፣ በመከላከልና የመሃል ሜዳዉን በመቆጣጠር የሲዳማ ቡና  ቡድን ሲበልጥ ወደ ጎል በመድረስና አጋጣሚዎችን በመፍጠር ድቻ የተሻለ  ነበር፡፡

በሁለተኛዉ የጨዋታ ክፍሌ ጊዜ የወላይታ ድቻ ቡድን ራሱን አደራጅቶ በመግባት በመከላከል፣  በማደራጀትና በማጥቃቱም የተሻለ ብልጫ የነበረው ቢሆንም ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡

የወላይታ ድቻ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ “ከሽንፈት የተመለስን በመሆናችን አንድ ነጥብ ማግኘታችን የሚያስከፋ ባይሆንም የፈጠርናቸው የጎል አጋጣሚዎች መጠቀም አለመቻላችንና በሜዳችን ሙሉ ነጥብ ያለመውሰዳችን ያስቆጫል” ብለዋል፡፡

received_1191117007636125-picsay

በአጨራረስ  ክፍተት እያስከፈላቸውን ያለውን ዋጋ ለመመለስ ተኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

Screenshot_2017-03-19-22-07-20-picsay

የሲዳማ ቡና አሰልጣኝ አለማየሁ አባይነህ (አለኮ) ” በመጀመሪያው የጨዋታ ከፍለ ጊዜ መጨረስ ሲገባን ያገኘናቸውን አጋጣሚዎች መጠቀም ያለመቻላችን ነጥብ እንድንጥል አድርጎናል” ብለዋል፡፡

ከሜዳቸው ውጭ  ተጫውተው አንድ ነጥብ ማግኘታቸው መልካም መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ዳኝነቱም የተሻለ መሆኑን ጠቁመዉ በሜዳዉ የተመለከቱት የስፖርታዊ ጨዋነት የተላበሰ የድጋፍ አሰጣጥ መቀጠል እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...