መነሻ ገጽ ወላይታ ድቻ የወላይታ ድቻ ቦርድ ትላንት እና ዛሬ በክለቡ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የወላይታ ድቻ ቦርድ ትላንት እና ዛሬ በክለቡ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

አጋራ
አጋራ

በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ወላይታ ድቻ ትናንት እና ዛሬ ሲመክር ውሎ በክለቡ አሰልጣኝ እና አመራሮች ላይ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሰረት የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሆሲሶ፣ ቴክኒካል ዳይሬክተሩ ታደሰ መታፈሪያና የደጋፊዎች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ አንዷለም ከሀላፊነታቸው ተነስተዋል፡፡

የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሆሲሶ

የወላይታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የወላይታ ድቻ ፕሬዝደንት አቶ ጎበዜ እንደገለጹት “አሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ ከክለቡ ጋር ውል ስላላቸው ወደ ስራቸው እንዲመለሱ ደብዳቤ ወጥቷል።” የክለቡ ፕሬዝዳንት አክለውም “የቦርዱ ውሳኔ በነገው መድረክም ይቀጥላል።” ብለዋል። በነገው እለት የሚኖሩትን ውሳኔዎች በትኩሱ የምናደርሳችሁ ይሆናል።

አሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ

ወላይታ ድቻ በዘንድሮው የሊጉ ጉዞ ካደረጋቸው 8ጨዋታዎች በ1 ብቻ በማሸነፍ በ3 አቻ ተለያይቶ በ4ቱ ተሸንፎ ማግኘት ከሚገባው 24ነጥቦች 6ቱን ብቻ በማሳካት የሊጉ ግርጌ ላይ ተቀምጧል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...