የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለረጅም አመታት የነበረውን የረጃጅም የስታዲዮም ሰለፎችን የሚያስቀርበት፣ የሚጭበረበሩ ትኬቶች የሚያጠፋበት ለሁሉም የእግር ኳስ አፍቃሪ እኩል እድል ሊፈጥር በሚችል ሁኔታ በዘመናዊ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ ከክፍያ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ጋር የውል ስምምነት አደረገ፡፡

ይህ ስምምነት ከ2010 ዓ.ም የውድድር ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን በመሆኑ ለክለቦች፣ ለደጋፊዎች፣ ለሚዲያ ባለሞያዎችና ባጠቃላይ ለአገራችን የእግር ኳስ እድገት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል፡፡
አስተያየት ይስጡ