መነሻ ገጽ አፍሪካ የኢትዮጵያ ተጋጣሚ በወዳጅነት ጨዋታ ቻድን ረታች
አፍሪካዜናዎች

የኢትዮጵያ ተጋጣሚ በወዳጅነት ጨዋታ ቻድን ረታች

አጋራ
አጋራ

የዛሬ ወር ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ አቻውን የሚገጥመው የኒጀር ብሔራዊ ቡድን ትናንት ምሽት በኒያሚ በተደረገ የወዳጅነት ጨዋታ ከዕረፍት በኋላ በተቆጠሩ ሁለት ግቦች የቻድ ብሔራዊ ቡድንን ሁለት ለምንም ረታ፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት ፈረንሳያዊውን አሰልጣኝ ዣን-ሚሸል ካቫሊን የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጋ መሾሟን ያሳወቀችው ኒጀር በዚህ ሳምንት ከቻድ እና ከሴራሊዮን ጋር ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን ለማድረግ ቀጠሮ መያዟ ቀድሞ የተነገረ ሲሆን የትናንት ምሽቱን የመጀመሪያ ጨዋታ በአሸናፊነት ደምድማለች፡፡ ድሉ ለአዲሱ አሰልጣኝ ዣን-ሚሸል ካቫሊም በኒጀር መለያ የመጀመሪያ ሆኖ ተመዝግቦላቸዋል፡፡

ትናንት ምሽት በጄኔራል ሴኚ ኩንቼ ብሔራዊ ስታዲየም የተደረገውን ጨዋታ ኒጀር ሁለት ለባዶ ስታሸንፍ ሁለቱም ግቦች ከዕረፍት መልስ በዛካሪ አደባዮር እና በኢሳ ጂብሪላ የተቆጠሩ ናቸው፡፡

ኒጀር ቀጣዩን የወዳጅነት ጨዋታ ማክሰኞ ምሽት 12፡00 ሰዓት በሃገር ውስጥ ሊግ ብቻ በሚጫወቱ ተጫዋቾቿ ከሴራሊዮንን ጋር ታደርጋለች፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...