መነሻ ገጽ CECAFAKE2017 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የሴካፋ ጉዞውን በድል ጀምሯል።
CECAFAKE2017ሪፖርትዋልያዎቹየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የሴካፋ ጉዞውን በድል ጀምሯል።

አጋራ
አጋራ

የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ደቡብ ሱዳንን በማሸነፍ የመጀመሪያ 3ነጥቡን ማሳካት ችሏል። 4-4-2 አሰላለፍን ምርጫው አድርጎ ወደ ሜዳ የገባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታው ሙሉ ለሙሉ ብልጫ ወስዶ እንደነበር በስፍራው የነበሩ ባልደረቦቻችን ገልፀውልናል። ለዋልያዎቹ የደደቢቱ ድንቅ ተጫዋች አቤል ያለው 2ግቦችን ሲያስቆጥር የቅ/ጊዮርጊሱ አቡበከር ሳኒ ቀሪዋን 1ግብ በማስቆጠር ዋልያዎቹ 3-0 በሆነ ውጤት እንዲያሸንፉ አስችለዋል። በጨዋታው 72% የኳስ ቁጥጥር የነበራቸው ዋልያዎቹ ከዚህም በላይ የግብ እድሎችን ፈጥሮ ተጨማሪ ግቦችን ማስቆጠር ይችል እንደነበር ምንጮቻችን ገልፀዋል።
በዚሁ ምድብ ትናንት የተገናኙት ኡጋንዳ እና ብሩንዲ ጨዋታቸውን 0-0 በሆነ አቻ ወጤት አጠናቀዋል። ጨዋታውን ተከትሎ ምድብ ለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ3 ነጥቦች መምራት ሲጀምር ። ኡጋንዳ እና ብሩንዲ እኩል 1 ነጥብ በመያዝ ሲከተሉ ደቡብ ሱዳን ያለምንም ነጥብ የምድቡ ግርጌ ላይ ተቀምጧል።
የምድብ ለ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ በካካሜጋ ስታዲየም ሀሙስ 9፡00 ሲል ኢትዮጵያ ከ ብሩንዲ እንዲሁም አርብ ዩጋንዳ ከ ደቡብ ሱዳን በተመሳሳይ 9፡00 ሲል ይጫወታሉ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ከሜሲ ጋር በአንድ ሜዳ የደመቀው የሜጀር ሊግ ሶከሩ ኮከብ ማረን ሀይለስላሴ

የማረን ሁለቱ ታናናሽ ወንድሞቹም እግር ኳስን ተጫውተዋል አሁን ላይስ ምን ላይ ናቸው።...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የእናቱን ሀገር መለያ የመልበስ ፍላጎት ያለው የግራ መስመር አጥቂ

ለአሜሪካ ከሀያ አመት በታች ብሔራዊ ቡድን የተጫወተው እና በዴንማርክ የሚገኘው ተጫዋች። እናቱ...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

“ኢትዮጵያን ባገለግል እጅግ ደስ ይለኛል” ወጣቱ ተጫዋች ጆሲሳ ስምዖን

በጀርመኑ ኮሎኝ የሚገኘው እና በቀጣዩ ክረምት ወደ ዋናው ቡድን የሚያድገው ወጣቱ የግራ...