መነሻ ገጽ ሴካፋ የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ላይ የሚሳተፉ 23 ተጫዋቾች ተለይተው ታወቁ።
ሴካፋዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ላይ የሚሳተፉ 23 ተጫዋቾች ተለይተው ታወቁ።

አጋራ
አጋራ

ከህዳር 24 ጀምሮ በኬንያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) የሚካፈለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ 23 ተጫዋቾችን ይፋ አድርጓል። በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ የሚመሩት ዋልያዎቹ ነገ(ሐሙስ) ጠዋት 2ሰዓት ላይ ወደ ኬንያ የሚያቀኑ ይሆናል።
በሁለት ምድብ ተከፍሎ በ10 ሀገራት መካከል ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው ይህ ውድድር በመጨረሻ ሰዓት በምድብ ለ የምትገኘው ተጋባዧ ሀገር ዚምባቡዌ ኬንያ ላይ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ ለተጫዋቾቹ አስተማማኝ ባለመሆኑ እራሳችንን አግልለናል በማለት በውድድሩ እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል።
በቡድኑ ውስጥ ከተካተቱት 27 ተጫዋቾች 4 ተጫዋቾች (አናጋው ባደግ ከድሬዳዋ ከተማ፣ ዮናስ ገረመው ከጅማ አባ ጅፋሩ፣ ኃይሌ እሸቱ ከአዲስ አበባ ከተማ እና መስዑድ መሀመድ ከኢትዮጵያ ቡና) የተቀነሱ ተጫዋቾች ናቸው።

ነገ ወደ ኬንያ የሚጓዘው ቡድን ዝርዝር

ግብ ጠባቂዎች
ታሪክ ጌትነት (ደደቢት)፣ በረከት አማረ (ወልዋሎ.አ.ዩ)፣ ተክለማርያም ሻንቆ (ሀዋሳ ከተማ)
ተከላካዮች
ቴዎድሮስ በቀለ (መከላከያ)፣ አበበ ጥላሁን (ሲዳማ ቡና)፣ አበባው ቡጣቆ (ቅ/ጊዮርጊስ)፣ ግርማ በቀለ (ኢትዮ-ኤሌክትሪክ)፣ አምሳሉ ጥላሁን (ፋሲል ከተማ)፣ ተመስገን ካስትሮ (አርባምንጭ ከተማ)፣ ኄኖክ አዱኛ (ጅማ አባ ጅፋር)

አማካዮች
ሳምሶን ጥላሁን (ኢትዮጵያ ቡና)፣ ተስፋዬ አለባቸው (ወልዲያ ከተማ)፣ ከነዓን ማርክነህ (አዳማ ከተማ)፣ እንዳለ ከበደ (አርባምንጭ ከተማ)፣ ብሩክ ቃልቦሬ (ወልዲያ ከተማ)፣ ፍሬው ሰለሞን (ሀዋሳ ከተማ)

አጥቂዎች
አቡበከር ሳኒ (ቅ/ጊዮርጊስ)፣ አብዱራህማን ሙባረክ (ፋሲል ከተማ)፣ አዲስ ግደይ (ሲዳማ ቡና)፣ ዳዋ ሁቴሳ (አዳማ ከተማ)፣ አማኑኤል ገብረሚካኤል (መቐለ ከተማ)፣ አቤል ያለው (ደደቢት)፣ ፀጋዬ ብርሀኑ (ወላይታ ድቻ)

ውድድሩ እሁድ ሲጀምር በምድብ ለ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሰኞ እለት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 8፡00 ሲል ከብሩንዲ አቻው ጋር የሚጫወት ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...