መነሻ ገጽ አፍሪካ ዜና | ወላይታ ዲቻ ለነገው ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዱን ዛሬ ሰርቷል።
አፍሪካካፍወላይታ ድቻዜናዎች

ዜና | ወላይታ ዲቻ ለነገው ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዱን ዛሬ ሰርቷል።

አጋራ
አጋራ

በአፍሪካ የክለቦች የኮንፌድሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ የሆነው ወላይታ ዲቻ ነገ(ረቡዕ) በ10 ሰአት ላለበት የመልስ ጨዋታው ዛሬ የመጨረሻ ልምምዱን አከናውኗል።

የአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪን ስንብት ተከትሎ በፕሪሚየር ሊጉ የተሻለ ውጤትን በማስመዝገብ ላይ የሚገኙት የክለቡ አዲሱ አሰልጣኝ ዘነበ ፍሰሀ ክለቡን እየመሩ በአፍሪካ የኮንፌድሬሽን ዋንጫ ላይ የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታውን ባለፈው ሳምንት በዛንዚባር አድርጎ ከሜዳው ውጭ 1 ለ 1 በመለያየት ወደ ሀገሩ መምጣቱ ይታወሳል። የመልስ ጨዋታውንም ለማድረግ ያለፉትን 7 ቀናት በሀዋሳ ልምምዱን ሲሰራ ቆይቶ ዛሬ ማለዳ የመጨረሻ ቀለል ያለውን ልምምዱን ሰርቷል።

አሰልጣኝ ዘነበ ከሀትሪክ ስፖርት ድረ-ገፅ ጋር ባደረጉት አጠር ያለ ቆይታ “በልዩ ትኩረት ወደ ሜዳ እንደሚገቡ ገልፀው በሜዳችን ነው ብለን አንዘናጋም በደጋፊያችን ፊት የተሻለ ግብ አስቆጥረን አሸንፈን የተሻለ ውጤት ይዘን ለመውጣት እንጥራለን ሜዳችን ቢሆንም አንዘናጋም” በማለት ተናግረዋል።

18 ተጫዋቾችን የያዘው ክለቡ ዚማሞቶን ከገጠሙበት ጨዋታ ምንም የተለየ ጉዳት በቡድኑ ውስጥ የሌለ ሲሆን ማረፊያቸውን ፓራዳይዝ ሆቴል በማድረግ የነገውን ጨዋታ እየጠበቁ እንደሆነ ተጫዋቾቹ ለድረገፃችን ገልፀዋል። አራቱም ዳኞች ከጎረቤት ጅቡቲ ሲሆኑ ኮሚሽነሩ ከሲሼልስ እንደሆኑ እና እስከ አሁን ግን ወደ ኢትዮጵያ እንዳልደረሱ ተገልፇል።

ጨዋታው ነገ(ረቡዕ) ልክ 10:00 ሲል በሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...