መነሻ ገጽ ወልዋሎ  ዋና አሰልጣኝ ለመቀጠር ሲያመነታ የቆየው ወልዋሎ አዲግራት በመጨረሻም  አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምን ቀጥሯል
ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

 ዋና አሰልጣኝ ለመቀጠር ሲያመነታ የቆየው ወልዋሎ አዲግራት በመጨረሻም  አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምን ቀጥሯል

አጋራ
አጋራ

ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ  አሰልጣኝ ብርሀኔ ገ/እግዚአብሔርን ቡድኑ ካስመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት ጋር ተያይዞ ከወር በፊት ማሰናበቱ እሚታወስ ነበር። የአሰልጣኙን መሠናበት ተከትሎ ቡድኑን ማን በኃላፊነት ይረከባል እሚለው በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል።

 የክለቡ የቦርድ አመራሮች አዲስ አሰልጣኝ ለመቅጠር ከ 7 እሚበልጡ አሰልጣኞች ጋር ግንኙነት ፈጥረው ለመደራደር ችለዋል። በመጨረሻም ከአርባምንጭ ከተማ ጋር በውጤት ቀውስ የተሰናበቱትን አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምን ቡድኑን እዲረከቡ በኃላፊነት ሾሟል።ቦርዱ አመሻሹን ላይ አሰልጣኙን መቀጠር ይፋ መሆኑን  ተክትሎ በአንዳንድ የክለቡ ደጋፊዎች ዘንድ እስከ አደባባይ ድረስ የዘለቀ ተቃውሞ መስማቱን ሀትሪክ ስፖርት ድህረ-ገጽ ከቦታው ልታረጋግጥ ችላለች።በተጨማሪም አዲሱ  አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም ለአንድ ዓመት  የውል ስምምነት እንደተፈራረሙ ክለቡ አስታውቋል።

አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም ከዚህ ቀደም በትራንስ ኢትዮጵያ፤ ሐረር ቢራ፤ ኢትዮጵያ ቡና ፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አርባምንጭ ከተማን ማሰልጠናቸው እሚታወስ ነው።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...