መነሻ ገጽ Uncategorized ኢትዮጵያ ቡና እና ካሳዬ አራጌ በይፋ ተፈራረሙ
Uncategorizedኢትዮጵያ ቡናዜናዎች

ኢትዮጵያ ቡና እና ካሳዬ አራጌ በይፋ ተፈራረሙ

አጋራ
አጋራ

ኢትዮጵያ ቡና እና ካሳዬ አራጌ በይፋ ተፈራረሙ

ከብዙ ዓመታት የአሜሪካ ቆይታ በኃላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ የቀድሞ ክለቡን ኢትዮጵያ ቡናን ለመያዝ በቃል ደረጃ ተስማምቶ የነበረው ካሳዬ አራጌ ዛሬ በይፋ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ተፈራርሟል።

በክረምቱ የተጨዋቾች ዝውውር ላይ በንቃት እየተሳተፋ ሚገኙት ቡናዎች እስካሁን ድረስ የ10 ተጨዋቾች ዝውውር አጠናቀዋል።ሁሉም ዝውውሮች በካሳዬ አራጌ እውቅና የተከናወኑ መሆናቸውን ካሳዬ ለክለቡ ኦፊሻል ፔጅ መግለጹ ሚታወስ ነው።

የክለቡ ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ከተናገሩት፦

“ያለፉትን ሁለት ዓመታት ከአዲሱ አሰልጣኝ ጋር ኢንፎርማል የሆነ ግንኙነት ስናደርግ ነበር።የውጭ አሰልጣኞችን አምጥተን አንዳንዶቹ ምንም አልጠቀሙንም፤ ስለዚህ ወደ ሀገር ውስጥ አሰልጣኝ ለመመለስ ወስነናል። ይህን ተከትሎ የቴክኒክ ኮሚቴ አቋቁመን ነበር፤ ኮሚቴውም የተለያዩ መስፈርቶችን አውጥቶ ካሳዬን መርጧል።ይህንን ተከትሎ ከአሰልጣኙ ጋር የተለያዩ ድርድሮች ስናደርግ ከርመን ዛሬ የፊርማ ስነ ስርዓቱን ለማድረግ ችለናል” ብለዋል።

በተጨማሪም አቶ ክፍሌ አማረ፦
“ካሳዬ በክለባችን ለ15 አመታት የተጫወተ እንዲሁም በ1994 እና 1995 ቡድኑን በተጫዋቾች አሰልጣኝነት የጥሎ ማለፍ ዋንጫ ያገኘ እና ስታዲየሞች ተራቁተው በነበረ ወቅት በራሱ የአጨዋወት ፍልስፍና ሚሊዮኖችን ወደ ስታዲየም የመለሰ ሰው ነው።
ደጋፊው ባለፉት ሶስት አመታት የክለቡ ውጤት አሽቆልቁሎ በነበረበት ወቅት ቡናን መልሱልን የሚል ተቃውሞ ሲያሰማ ነበር፤ ይህንን ተከትሎ ካሳዬን ወደ አሰልጣኝነት ማምጣቱ በደጋፊው ስም እናመሰግናለን” በማለት ደጋፊውን ወክለው ሃሳባቸውን ገልፀዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...