መነሻ ገጽ ኢትዮጵያ ቡና ​አዲሱ የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ኮስታዲን ፓፒች ከቡና ጋር ውል እያለባቸው  ለደቡብ አፍሪካው ሮያል ኤግልስ ፈረሙ
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎች

​አዲሱ የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ኮስታዲን ፓፒች ከቡና ጋር ውል እያለባቸው  ለደቡብ አፍሪካው ሮያል ኤግልስ ፈረሙ

አጋራ
አጋራ

ኢትዮጵያ ቡና ዘንድሮ አሰልጣኝ ፖፓዲች ክለቡን በክረምት ዝግጅት እና በደቡብ ካስትል ዋንጫ ላይ ከመሩ በኃላ ከአዲስ ከተማ ዋንጫ ጀምሮ በህመም ምክንያት ክለቡን ከለቀቁ በኃላ ሌላኛውን ሰርቪያዊ አሰልጣኝ ኮስታዲን ፓፒችን ወደ ክለቡ በማምጣት አስፈርመው ነበር፡፡አሰልጣኙ ክለቡን ይዘው እያሰለጠኑ ቆይታ በማድረግ ሦስት ጨዋታዎችን የመሩ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ ግን የቤተሰብ ችግር አለብኝ ወደ ሀገሬ ሄጄ እመለሳለሁ በሚል  ነበር ከሀገር መውጣት የቻሉት አሁን ግን ከወደ ደቡብ አፍሪካ እየወጡ ባሉ መረጃዎች ከሆነ አሰልጣኙ ለደቡብ አፍሪካው የቀድሞ ክለባቸው ሮያል ኤግል ፊርማቸውን አኑረዋል ተብሏል፡፡ በተለይ ለክለቡ ቅርበት ያላቸው የደቡብ አፍሪካ  ድህረ ገፆች አሰልጣኙ  በውጤት ቀውስ ውስጥ፡ለሚገኘው ሮያል ኤግልስ መፈረማቸው አስታውቀዋል ፡፡ 

አሰልጣኙ በሮያል ኤግልስ ከዚህ ቀደም በነበራቸው ውጤት ታይቶ  በትናንትናው እለት ሰኞ ፊርማቸውን ለክለቡ ያኖሩት፡፡ አሰልጣኙ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር የውል ኮንትራት እያላቸው አሰልጣኙ በዚህ አይነት አወዛጋቢ ድርጊት ላይ መፈረማቸው ተቃውሞን ያስነሳ ሲሆን በቀጣይም ክለቡ ለ CAF  ደብዳቤ እንደሚልክ ታውቋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...