መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና አስተያየት| ወልቂጤ ከተማ 0-1 ሲዳማ ቡና
ሲዳማ ቡናወልቂጤ ከተማዜናዎችየአሰልጣኞች አስተያየትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አስተያየት| ወልቂጤ ከተማ 0-1 ሲዳማ ቡና

አጋራ
አጋራ

👉👉ሜዳው የሚያስገድደውን አድርገናል ዘርዓ ሙሉ (ሲዳማ ቡና)

👉👉 ያገኘናቸውን የግብ እድሎች አለመጠቀማችን በዛሬው ጨዋታ ዋጋ አስከፍሎናል ደጋአረግ ይገዙ (ወልቂጤ ከተማ)

 

14ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በሁለት ቀሪ ጨዋታዎች ዛሬ ፍፃሚያቸውን ሲያገኙ ወልቂጤ ወልቂጤ ከተማ ሲዳማ ቡናን አስተናግዶ 1-0 ከተሸነፉ በኋላ የሁለቱም ቡድን አሰልጣኞች አስተየያታቸውን ሰጥተዋል።

ሜዳው የሚያስገድደውን አድርገናል ዘርዓ ሙሉ (ሲዳማ ቡና)

ስለጨዋታው

ሜዳው የሚያስገድደውን አድርገናል። ኳስ ይዞ ለመጫወት ምቹ ስላልሆነ ስለዚህ ያለው አማራጭ ዛሬ የተጫወትነው አጨዋወት ከአጨዋወታችን ውጪ ነው። ኳሶን ከሜዳችን ቶሎ ቶሎ ማውጣት። ያገኘነውን አጋጣሚ ግብ ማድረግ ነበር ደግሞም ተሳክቶልናል። እናም በተጫዋቾቼ በጣም ኮርቻለው ምክንያቱም በታክቲካል ዲሲፕሊን ሙሉ 90 ደቂቃ ጥሩ ነበሩ። እነሱ ሜዳውን ስለሚያውቁት በሚገባ ረጃጅም ኳሶችን ነው ሚጫወቱት። እሱን ተቆጣጥረን የነሱን ተጫዋቾች ስላቆምናቸው ውጤት ይዘን እንድንወጣ አግዞናል።


ያገኘናቸውን የግብ እድሎች አለመጠቀማችን በዛሬው ጨዋታ ዋጋ አስከፍሎናል ደጋአረግ ይገዙ (ወልቂጤ ከተማ)

ስለጨዋታ

ጨዋታው እንዳያችሁት ነው። ባሰብነው መንገድ መከወን አልቻልንም። በተለይ የመጀመሪያው 45 ተጫዋቾቼ ጨዋታውን አሸንፈው ለመውጣት ከፍተኛ ጉጉት ውስጥ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ቀስ ብሎ ወደ ፊት ለመንቀሳቀስ ተቸግረን ነበር። ሁለተኛ አጋማሽ ላይ ግን ከመጀመሪያው አጋማሽ የተለየ እንደነበር አንተም የተመለከትከው ነው። ያገኘናቸውን የግብ እድሎች አለመጠቀማችን በዛሬው ጨዋታ ዋጋ አስከፍሎናል። እነሱ አንድ ድል ፈጥረው በሚገባ ተጠቅመው አሸንፈዋል እኛ ደግሞ ነጥብ አጥተናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...