መነሻ ገጽ ኢትዮጵያ ቡና አስተያየት| ኢትዮጵያ ቡና 1-1 ወልቂጤ ከተማ
ኢትዮጵያ ቡናወልቂጤ ከተማየአሰልጣኞች አስተያየትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አስተያየት| ኢትዮጵያ ቡና 1-1 ወልቂጤ ከተማ

አጋራ
አጋራ

👉👉 “ስትራቴጂ መቀየር ካስፈለገ ኳስ ተጫዋች መለወጥ ያስፈልጋል” (ካሳዩ አራጌ ኢትዮጵያ ቡና)

👉👉 ለጨዋታው ይዘነው የገባነው አጨዋወት ተጫዋቾቼ ለመተግበር የሚችሉትን ያህል ጥረት አድርገዋል (ደግአረግ ይግዛው ወልቂጤ ከተማ)

13ኛ ሳምንት ዛሬ ፍፃሜውን ሲያገኝ። ኢትዮጵያ ቡና ወልቂጤ ከተማን አስተናግዶ 1-1 ከተጠናቀቀ በኋላ ሁለቱም ቡድኖች ለብዙሀን መገናኛ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

“ስትራቴጂ መቀየር ካስፈለገ ኳስ ተጫዋች መለወጥ ያስፈልጋል” (ካሳዩ አራጌ ኢትዮጵያ ቡና)

ስለጨዋታው

“ጨዋታው በአጠቃላይ ጥሩ ነው። በአጠቃላይ የምለው ነገር ሂደቱን መታገስ ይገባል። በየሰከንዱ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል መድረስ አይቻልም። መድረስ ይቻላል ግን አስተማማኝ አይደለም። ይሄ ነው ተጫዋቾች ላይ ጫና የፈጠረው። ተጫዋቾቹ በነፃነት እንዲጫወቱ ማድረግ አለብን። ከውጤት መራራቅ ስላለ በሁለተኛው አጋማሽ መጣደፍ ውስጥ ገብተዋል። የመጀመሪያው አጋማሽ ላይ ተጭነን ተጫውተናል። በሁለተኛው አጋማሽ የኛ ሜዳ ላይ ተጭነው ተጫውተዋል። በዚህ አይነት መንገድ ሲመጣ ለመውጣት ይቸግራል። በዛ ሰዓት በሚኖሩ ሂደቶች የሚበላሹ ኳሶች ይኖራሉ።”

ቡና ሁለተኛ ስትራቴጂ አያስፈልገውም ?

“ሁለተኛ ስትራቴጂ የሚባለው ነገር የተጫዋች ለውጥ ያስፈልጋል። ስትራቴጂ መቀየር ካስፈለገ ኳስ ተጫዋች መለወጥ ያስፈልጋል።”
ስለጨዋታው

ለጨዋታው ይዘነው የገባነው አጨዋወት ተጫዋቾቼ ለመተግበር የሚችሉትን ያህል ጥረት አድርገዋል (ደግአረግ ይግዛው ወልቂጤ ከተማ)

ስለጨዋታው

እንግዲህ ለፕሪምየር ሊጉ እንግዳ እንደመሆናችን መጠን። ጠንካራ ጨዋታ ነበር። ቡና ትልቅ ደጋፊ ያለው ክለብ ነው። ለጨዋታው ይዘነው የገባነው አጨዋወት ተጫዋቾቼ ለመተግበር የሚችሉትን ያህል ጥረት አድርገዋል። በርግጥ በመጀመሪያው አጋማሽ እንፈለግነው መንቀሳቀስ አልቻልንም። በሁለተኛው አጋማሽ ግን ችግሮቻችንን ፈተን በተቻለን መጠን ተጭነን ለመጫወት ያደረግነው ጥረት ቢኖርም።ባሰብነው ልክ ደግሞ ግብ ማግኘት አልቻልንም። በአጠቃላይ ግን ከጠንካራው ቡና ጋር ቢሆንም። ተጫዋቾቼ ባደረጉት እንቅስቃሴ ለወደፊቱ ተስፋ የሚሰጥ ነው። በቀጣይ ድክመቶቻችን እያየን ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነን እንቀርባለን።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...