መነሻ ገጽ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ2010 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ወልዋሎ አ.ዩ የፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ነጥቡን አስመዘገበ፡፡
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

በ2010 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ወልዋሎ አ.ዩ የፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ነጥቡን አስመዘገበ፡፡

አጋራ
አጋራ

በ2010 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ሁለተኛ ቀን አንድ ጨዋታ ዛሬ ሲድረግ ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ ከፋሲል ከተማ ተገናኝተው ጨዋታቸውን 2-2 በሆነ ውጤት አጠናቀዋል። ግብ በማግባቱ ረገድ ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ ቀዳሚ ሲሆን በ5ኛው ደቂቃ በሙሉዓለም ጥላሁን (ፍ.ቅ.ም) እንዲሁም 44ኛው ደቂቃ ላይ በከድር ሳለህ ያስቆጠሯቸው ግቦች መሪ መሆን ችሎ ነበር። ከእረፍት መልስ ፋሲል ከነማ 61ኛው ደቂቃ ላይ በሰኢድ ሀሰን እና 90ኛው ደቂቃ ላይ በአይናለም ሃይሉ ባስቆጠሯቸው ግቦች ከሜዳው ውጪ 1ነጥብ ይዞ መመለስ ችሏል።

ፕሪምየር ሊጉ ነገ(ሰኞ) ሲቀጥል ደደቢት ከ ወላይታ ዲቻ ማክሰኞ ደግሞ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከ መከላከያ በተመሳሳይ 11፡30 ሲል በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚጫወቱ ይሆናል፡፡ ለብሔራዊ ቡድኑ 3 እና ከዛ በላይ ተጫዋቾችን ያስመረጡት ቅ/ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ከተጋጣሚዎቻቸው ጋር የሚያደርጏቸው ጨዋታዎች ቀንና ሰዓት ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
የፎቶው ምንጭ ፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ / fasil kenema football club ፌስቡክ ገጽ

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...