በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) ኢትዮጵያ ስምንት ደረጃዎችን በማሽቆልቆል 145ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ኢትዮጵያ መጋቢት ወር ላይ ከነበረችበት 137ኛ ደረጃ 8 በማሽቆልቆል ነው 145ኛ ደረጃን የያዘችው፡፡
ከአፍሪካ ደግሞ 41ኛ ደረጃ ላይ መሆኗን ፊፋ በድህረገፁ አስፍሯል።
ቱኒዚያ ዘጠኝ ደረጃዎችን በማሻሻል በዓለም 14ኛ ላይ የተቀመጠች ሲሆን ከአፍሪካ አንደኛ ሆናለች።

ሴኔጋል አንድ ደረጃ በመቀነስ ከዓለም 28ኛ ከአፍሪካ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ስትይዝ፥ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ከዓለም 38ኛ ከአፍሪካ 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በአፍሪካ ደረጃ
ሞሮኮ፣ ግብፅ፣ ናይጀሪያ፣ ካሜሩን፣ ጋና፣ ቡርኪናፋሶና ኬፕ ቨርዴ በቅደም ተከተል ከ4ኛ እስከ 10ኛ ያለን ደረጃ ይዘዋል።
ባለፈው ወር ከነበሩበት በዚህ ወር ብዙ ያሽቆለቆሉ ሀገራትም ይፋ ሆነዋል፤ ሃይቲ 23፣ ፓፑዋ ኒው ጊኒ 21 እንዲሁም ኒካራጓ 20 ደረጃዎችን ዝቅ ብለዋል።
በፊፋ ወርሃዊ ሰንጠረዥ ቶንጋ፣ ሶማሊያ፣ ኤርትራ፣ ባህማስ እና አንጉሊያ የመጨረሻውን 207ኛ ደረጃ ይዘዋል።
አስተያየት ይስጡ