በ6ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 6ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መካከል ወደ ድሬዳዋ ያቀናው አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርቶ መመለስ ችሏል፡፡
ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ከ 5 ጨዋታዎች 4ቱን ጨዋታዎች አቻ በመውጣት በአንዱ በማሸነፍ በ7 ነጥብ 7ተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ በአንፃሩ ተጋጣሚው አዳማ ከተማ ከ6 ጨዋታዎች 2 አሸነፎ በ3አቻ ፣በ1ሽንፈት በሊጉ ሰንጠረዥ 4ኛ ደረጃ ላይ ሊቀመጥ ችሏል፡፡
በሌላ ጨወታ ፋሲለደስ ስታዲየም ላይ ወላይታ ድቻን ያስተናገደው ፋሲል ከተማ በ66ኛ ደቂቃ ላይ በተከላካዩ አይናለም ሀይለ የግንባር ግብ በዘንድሮ አመት በኮንፌዴሬሽኑ ኢትዮጵያን እሚወክለው ወላይታ ድቻን 1-0 መርታት ችሏል፡፡
በዚህ መሠረት ፋሲል ከተማ በ9ነጥብ በሰንጠረዡ 3ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ በአንፃሩ ወላይታ ድቻ በ5ነጥብ በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ 13ኛ ላይ መቀመጥ ግድ ሆኖበታል፡፡
*ፎቶ ፋሲል ከተማ የፌስቡክ ገጽ
አስተያየት ይስጡ