መነሻ ገጽ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በኢትየጵያ ፕሪምየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ይደረጋሉ።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

በኢትየጵያ ፕሪምየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ይደረጋሉ።

አጋራ
አጋራ

በኢትየጵያ ፕሪምየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሲቀጥሉ ነገ (ቅዳሜ) 3 ጨዋታዎች እንዲሁም ከነገ በስቲያ (እሁድ) 5 ጨዋታዎች የሚደረጉ ይሆናል።

ነገ በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ አዲግራት ላይ ካደረጋቸው 2 ጨዋታዎች ሁለቱንም በአቻ ውጤት ያጠናቀቀው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሲዳማ ቡናን ሲያስተናግድ በሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲን ስታድየም ወልድያ ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ ይጫወታሉ። ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቻን ዝግጅት 3 ተጫዋቾችን በማስመረጡ ምክንያት ምንም የሊጉን ጨዋታ ማከናወን ያልቻለው ኢትዮጵያ ቡና በሁለተኛው ሳምንት ሳይጠበቅ ሜዳው ላይ በወላይታ ድቻ የ1-0 ሽንፈት ያስተናገደውን መከላከያን 11:30 ሲል አ/አ ስታዲየም ላይ ያስተናግዳል።

ፕሪምየር ሊጉ እሁድ ሲቀጥል 4ጨዋታዎች በተመሳሳይ 9 ሰዓት ሲደረጉ ቅ/ጊዮርጊስ መቐለ ከተማን የሚያስተናግድበት ጨዋታ 11:30 ላይ ይደረጋል። ካደረጋቸው 2 ጨዋታዎች ሁለቱንም በአቻ ውጤት ያጠናቀቀው አርባምንጭ ከተማ 1 ነጥብ ያለውን ኢትዮ-ኤሌክትሪክን ያስተናግዳል። በጅማ ስታዲየም 3 ነጥቦችን ይዞ በሊጉ 3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ጅማ አባጅፋር 1 ነጥብ ይዞ በሊጉ 10ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ፋሲል ከተማ ሲያስተናግድ ቦዲቲ ላይ የሊጉ መሪ ወላይታ ድቻ 1 ነጥብ ያለውን አዳማ ከተማን ያስተናግዳል። እዚህ አ/አ ላይ በ9፡00 በሁለተኛው ሳምንት ወደ አዳማ ተጉዞ ከአዳማ ከተማ ጋር ያለግብ አቻ ተለያይቶ የተመለሰው ደደቢት በሁለተኛው ሳምንት ወልድያ ከተማን በሰፊ ውጤት ያሸነፈውን ሐዋሳ ከተማን ያስተናግዳል። 11:30 ሲል እንደ ኢትዮጵያ ቡና ሁሉ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቻን ዝግጅት 10 ተጫዋቾችን በማስመረጡ ምክንያት ምንም የሊጉን ጨዋታ ማከናወን ያልቻለው የአምናው ሻምፒዮን ቅ/ጊዮርጊስ አዲስ አዳጊውን መቐለ ከተማን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል።
ፕሪምየር ሊጉን ወላይታ ድቻ በ4 ነጥቦች ሲመራ ምንም ጨዋታ ያላደረጉት ኢትዮጵያ ቡና እና ቅ/ጊዮርጊስ የሊጉ ግርጌ ላይ ይገኛሉ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ድንቅ የቅጣት ምቶች በነበሩት ጨዋታ ነገሌ ሲያሸንፍ ሀዋሳ በወልዋሎ ነጥብ ጥሏል

7 ጎሎች እና ሁለት ድንቅ የቅጣት ምት ጎሎች በነበሯቸው ሁለት ጨዋታዎች ነገሌ...