መነሻ ገጽ Uncategorized በኘሪሜየር ሊጉ ደደቢት አቻ ሲለያይ የደረጃ ተከታዪ ሲዳማ ቡና ተሸንፈዋል
Uncategorizedየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

በኘሪሜየር ሊጉ ደደቢት አቻ ሲለያይ የደረጃ ተከታዪ ሲዳማ ቡና ተሸንፈዋል

አጋራ
አጋራ

 

 

picsart_1488459392107.jpg

በ23ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ቀጥለው ተደረገዋል፡፡

በመብራት መቆራረጥ ምክንያት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ አዲስአበባ ስታዲየም እሚደረጉ  የ9 ሰዓት ጨዋታዎችን 30ደቂቃ ቀደም ብለው እንዲጀመሩ ማደረጉን ተከትሎ፡፡ 8:30 ላይ በተደረገ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከፋሲል ከተማ ሲገናኙ ፋሲል ከተማዎች አጥቂው ኤዶም ሆውሶሮቪ ከዕረፍት መልስ ባስቆጠራት ጎል 1 ለ 0 አሸንፈው ውጥተዋል።

 

ወልድያ ላይ ወልድያ ከወላይታ ዲቻ ያደረጉት ጨዋታ በወልድያ 1 ለ 0 አሸናፊነት ሲጠናቀቅ ሃብታሙ ሸዋለም ግቧን አስቆጥሯል።

አርባ ምንጭ ከተማ ላይ በ ጨዋታ ባለሜዳው አርባምንጭ ከተማ በድሬዳዋ ከተማ ሁለት ለባዶ ተሸነፏል፡፡

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ በ40ኛው ደቂቃ ላይ የድሬዳዋ ከነማው ዮሴፍ ዳሙዬ ባስቆጠራት ግብ 1-0 እየመራ ለእረፍት ወጥተዋል።

ከዕረፍት መልስም በ86ኛው ደቂቃ የድሬዳዋ ከነማ 18 ቁጥሩ በረከት ይስሃቅ ሁለተኛውን ጎል በማስቆጠር ቡድኑ የጨዋታ የበላይነቱን እንደያዘ ውድድሩን እንዲያጠናቅቅ አደርጓል።

በጨዋታው  ድሬዳዋ ከተማዎች ፍጹም የጨዋታ የበላይነትን ያሳዩበት ሲሆን በአንጻሩ አርባምንጭ ከተማ ደግሞ በሜዳው በተከታታይ ሁለት ጊዜ በመሸነፍ ስጋት ውስጥ ገብቷል ፡፡

 

ሃዋሳ ላይ ሃዋሳ ከሲዳማ ቡና ያደረጉት ጨዋታ በሃዋሳ 3 ለ 2 አሸናፊነት ፍጻሜውን አግኝቷል።

 

ጃኮ አረፋት፣ ፍሬው ሰለሞን እና ታፈሰ ሰለሞን ለሃዋሳ ጎሎችን ሲያሰቆጥሩ አዲስ ግደይ ደግሞ ለሲዳማ ቡና ሁለቱን ጎሎች ከመረብ አገናኝቷል።

 

ጅማ ላይ የተደረገው ጅማ አባ ቡና ከአዳማ ከተማ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ሲጠናቀቅ፥ በድሉ መርዕድ ለጅማ አባ ቡና ዳዋ ሁቴሳ ደግሞ ለአዳማ ከተማ ጎሎቹን አስቆጥረዋል።

 

10:30 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የተደረገው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ደደቢት ጨዋታ ብቸኛው ጎል ያልተቆጠረበት ጨዋታ በመሆን አቻ ተጠናቋል።

የደረጃ ሰንጠረዥ ይመልከቱ

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...