መነሻ ገጽ ቅድመ ዳሰሳ ቅድመ ዳሰሳ | ወላይታ ድቻ ከኢትዮ-ኤሌክትሪክ
ቅድመ ዳሰሳኢትዮ-ኤሌክትሪክወላይታ ድቻየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ዳሰሳ | ወላይታ ድቻ ከኢትዮ-ኤሌክትሪክ

አጋራ
አጋራ

የኢትየጵያ ፕሪምየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት የዕለተ ሰኞ ጨዋታ ቅድመ ዳሰሳ

በኢትየጵያ ፕሪምየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ(ሰኞ) በሚደረጉ 2 የክልል ጨዋታዎች ፍፃሜውን ያገኛል። የዚህ ቀን ሁለቱም ጨዋታዎች በሊጉ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኙትን 4ቡድኖች የሚያገናኙ ይሆናል።

ሶዶ ላይ አስከፊ የውድድር ጊዜን እያሳለፉ የሚገኙት ወላይታ ድቻ እና ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሚጫወቱ ይሆናል። ወላይታ ድቻ በክለቡ 8አመታት ያሳለፉትን አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪን ካሰናበተ በኋላ በቀድሞ የክለቡ ከ17 አመት በታች አሰልጣኝ በነበረው ዘነበ ፍሰሀ እየተመራ ወደሜዳ የሚገባ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በበኩሉ አሰልጣኝ ብርሀኑ ባዩን አሰናብቶ በቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ኢትዮ-ኤሌክትሪክን ይዘው የመጀመሪያ ጨዋታችውን ያደርጋሉ።


በ8ኛው ሳምንት ጨዋታ ወላይታ ድቻ ወደ ይርጋለም ተጉዞ ሲዳማ ቡናን ገጥሞ በአለማየሁ አባይነህ ቡድን የ3-1 ሽንፈት አስተናግዶ ነው ወደ ወልድያ የተጓዘው። ውጤቱንም ተከትሎ ወላይታ ድቻ 5ነጥቦችን ብቻ በመሰብሰብ የሊጉ ግርጌ ላይ ይገኛል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአንፃሩ በ8ኛው ሳምንት የሊጉን መሪ ደደቢትን አስተናግዶ በተመሳሳይ 3-1 መሸነፉ ይታወሳል። ባሳለፍነው ረቡዕ የ2ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታውን ከኢትዮጵያ ቡና ጋር አድርጎ 2-1 ድል በማድረግ ወደ አሸናፊነት ተመልሶ ወደ ሶዶ ተጉዟል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በሊጉ 8ነጥቦችን ይዞ ከወራጅ ቀጠናው በ3 ነጥቦች ርቆ 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
በወላይታ ድቻ በኩል የተሰማ አዲስ የጉዳት ዜና የሌለ ሲሆን በኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኩል ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ሲጫወቱ ጉዳት ያስተናገዱት ተከላካዩ አወት ገ/ሚካኤል እና አጥቂው ቢንያም አሰፋ ከቡድኑ ጋር ወደ ሶዶ ባለመጓዛቸው በዛሬው ጨዋታ የማይሳተፉ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ድንቅ የቅጣት ምቶች በነበሩት ጨዋታ ነገሌ ሲያሸንፍ ሀዋሳ በወልዋሎ ነጥብ ጥሏል

7 ጎሎች እና ሁለት ድንቅ የቅጣት ምት ጎሎች በነበሯቸው ሁለት ጨዋታዎች ነገሌ...