መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቫዝ ፒንቶ ተለያዩ።
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቫዝ ፒንቶ ተለያዩ።

አጋራ
አጋራ

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ የሆነው እና በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ አንጋፋው ክለብ ቅ/ጊዮርጊስ እና ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ቫዝፒንቶ በዛሬው እለት መለያየታቸውን የቅ/ጊዮርጊስ ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ አሳውቋል።። አሰልጣኙ በቅ/ጊዮርጊስ ለ1 አመት ብቻ የቆዩ ሲሆን በእርሳቸው የአሰልጣኝነት ዘመን ክለቡ ከ4 ተከታታይ አመታት ሻምፒዮንነት በኋላ በ2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ በኢትዮጵያ ዋንጫ(በጥሎ ማለፍ) ደግሞ በመከላከያ ተሸንፎ ሁለተኛ ወጥቷል። ይህንንም ተከትሎ ክለቡ ከ2006 ዓ.ም በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአፍሪካ ውድድሮች ውጪ የሆነበትን ታሪክ ያስመዘገበው በእኚሁ አሰልጣኝ ነው። አሰልጣኙ በክለቡ በነበራቸው ቆይታ ቅ/ጊዮርጊስን ኳስ ተቆጣጥሮ የሚጫወት ቡድን ለማድረግ እና ደጋፊው የሚፈልገው አይነት አጨዋወት ለመጫወት ጥረት ሲያደርጉ ተስተውሏል። ሆኖም ክለቡ የ2011 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጅማሬውን በሚያደርግበት እለት ከአሰልጣኙ ጋር መለያየቱ የክለቡን ደጋፊዎች። እና ብዙውን የእግርኳስ ተመልካቾች ግርምት ውስጥ ከቷል። ክለቡም ከተለያዩ አሰልጣኞች ጋር ንግግር እያደረገ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...