መነሻ ገጽ ዜናዎች መቐለ ከተማ ከ5 ተጫዋቾች ጋር በስምምነት ተለያይቷል 
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

መቐለ ከተማ ከ5 ተጫዋቾች ጋር በስምምነት ተለያይቷል 

አጋራ
አጋራ

በዘንድሮው የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እሚገኘው መቐለ ከተማ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ካስፈረማቸው 3 አዲስ ተጫዋቾችና ከሁለት  ነባር ተጫዋቾች ጋር በስምምነት ክለቡ አሰናብቷቸዋል ።
ከተሰናበቱት ተጫዋቾች መካከል ዱላ ሙላቱ(ከሀዲያ ሆሳዕና የፈረመ) ፣ዮሱፍ ደንገቶ (ከወላይታ ድቻ የፈረመ)፣ሙሉጌታ ረጋሳ (ከወልዲያ የፈረመ)፣ዮሴፍ ሀይሉ (ነባር )፣ ተመስገን አዳሙ (ነባር) ከነዚህ ተጫዋቾች ጋር የ3ወር ደሞዝ በመክፈል በስምምነት መለያየቱ ክለቡ ለሀትሪክ ስፖርት ድህረ-ገፅ አስታውቋል።

ክለቡ  አምስቱን  ተጫዋቾች ለማሰናበት የተገደደው እሚፈለገውን  ግልጋሎት ሊሰጡት ባለመቻላቸው መሆኑን አያይዞ ገልጿል። 

መቐለ ከተማ  በአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌ እየተመራ ካደረጋቸው 13 ጨዋታዎች በስድስት ጨዋታ ድል ሲቀናው በስድስት ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቆ በአንድ  ጨዋታ ብቻ  ሽንፈት አስተናግዶ ከመሪው ደደቢት በአንድ ነጥብ ተበልጦ በ24 ነጥብ  በደረጃ ሰንጠረዡ 2ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።

  

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...