By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ሾለ እኛ
Reading: ሀትሪክ አበይት | የ17ኛ ሳምንት ዋና ዋና ጉዳዮች
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ሾለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ሾለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
Š 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችሀትሪክ አበይት ጉዳዮች

ሀትሪክ አበይት | የ17ኛ ሳምንት ዋና ዋና ጉዳዮች

ዳዊት ታደሰ
ዳዊት ታደሰ 6 years ago
Share
SHARE

👉👉 ተጠባቂው ጨዋታ ያለግብ ተጠናቋል።

👉👉ቅዱስ ጊዮርጊስ በዚህ አመት ለመጀመሪያ ግዜ በተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ሸንፈት አስተናግዷል።

👉👉አዳማ ከተማ በአመቱ የመጀመሪያውን የሜዳ ውጭ ድል አሳክቷል።

👉👉ሙጂብ ቃሲም ለተከታታይ ሶስት ጨዋታዎች ግብ ሳያስቆጥር ወጥቷል።

- ማሰታውቂያ -

👉👉ሳልሀዲን ሰይድ በደጋፊዎች ጥቃት ደርሶበታል

👉👉ግቦች

👉👉ውጤቶች

👉👉የደረጃ ሰንጠረዥ

👉👉ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች

 

ተጠባቂው ጨዋታ ያለግብ ተጠናቋል።

አርብ ትግራይ ስታዲዮም ላይ የተደረገው የመቐለ 70 እንደርታ እና ባህርዳር ከነማ ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። የባህርዳር ከነማ ደጋፊዎች ክለባቸውን ለመደገፍ ወደ መቐለ ሲገቡ በመቐለ 70 እንደርታ ደጋፊዎች ደማቅ አቀበባል የተደረገላቸው ሲሆን ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላም የእራት ግብዣ ተደርጎላቸዋል። ይህ የደጋፊዎች ሰላማዊ መንፈስ ለእግር ኳሱ መልካም ገፅታ ከመፍጠር አኳያ ሊበረታታ የሚገባው ነው።

ቅዱስ ጊዮርጊስ በዚህ አመት ለመጀመሪያ ግዜ በተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ሸንፈት አስተናግዷል።

ዋና አሰልጣኙን እና ረዳቶችን ማገዱን ተከትሎ በሲኒየር ተጫዋቾች እየተመሩ ጨዋታውን ያደረጉት ቅዱስ ጊዮርጊሶች 34ኛው ደቂቃ ላይ አስቻለው ግርማ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ሸንፈት አስተናግደዋል። ከሳምንት በፊት ፈረሰኞቹ በወልቂጤ ከተማ ሽንፈት አስተናግደው እንደነበር የሚታወስ ነው።

አዳማ ከተማ በአመቱ የመጀመሪያውን የሜዳ ውጭ ድል አሳክቷል።

በፌደሬሽኑ በተጣለበት ቅጣት ምክንያት ሁለት ጨዋታዎችን ከሜዳው ውጭ እንዲያደርግ የተወሰነበት ወልቂጤ ከተማ በአዳማ ከተማ 2-0 ሽንፈት ቀምሷል። ወልቂጤ ላይ ድል የተቀዳጁት አዳማ ከተማዎች በዚህ አመት ከሜዳቸው ውጭ ያሳኩት የመጀመሪያው ሶስት ነጥብ ሆኗል። ለአዳማ ከተማ ከነዓን ማርክነህ እና በረከት ደስታ የማሸነፍያውን ግብ ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

5 ጨዋታዎች በአመቱ በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል።

በዚህ ሳምንት ከተደረጉት 8 ጨዋታዎች አምስቱ በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል። ይህ ደግሞ በሊጉ የ17 ሳምንታት ጉዞ በ1ሳምንት ጨዋታዎች በርካታ የአቻ ውጤቶች የተመዘገበበት ሳምንት ያደርገዋል።

ሙጂብ ቃሲም ለተከታታይ ሶስት ጨዋታ ግብ ሳያስቅጥር ወጥቷል።

የፋሲል ከነማው አጥቂ እና ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በ14 ግቦች በመምራት ላይ የሚገኘው ሙጂብ ቃሲም ለተከታታይ ሶስት ጨዋታዎች ግብ ሳያስቆጥር ወጥቷል። በ14ኛው ሳምንት አፄዎቹ ቅዱስ ጊዮርጊስን አስተናግደው 2-2 በተለያዩበት ጨዋታ ግብ ያስቆጠረው አጥቂው ባለፉት ሳምንታት ግብ ማስቆጠር ተስኖታል።

ሰልሀዲን ሰይድ በደጋፊዎች ጥቃት ደርሶበታል

ፈረሰኞቹ ሽንፈት ካስተናገዱበት የሰበታ ጨዋታ በኋላ ሁለት የክለቡ ደጋፊዎች የፊት መስመር አጥቂውን መትተውታል። ተጫዋቹ 62ኛው ደቂቃ ላይ በእለቱ ዳኛ ከሜዳ በቀይ ካርድ የተወገደ ሲሆን በቀይ ካርዱ የተበሳጨው ተጫዋቹም በደጋፊዎቹ ከተመታ በኋላ ክቡር ትሪቡን አካባቢ የሚገኘውን መስኮት በስሜታዊነት መትቶ ጉዳት አስተናግዶ ወደ ቤተዛታ ሆስፒታል ተወስዶ የህክምና እርዳታ ተደርጎለት ማምሻውን ወጥቷል።

ግቦች

በ 17ኛ ሳምንት 10 ግቦች ተቆጥረዋል። ይህ ማለት ደግሞ 1.25 በአማካይ ተቆጥረዋል ማለት ነው። ባለፈው ሳምንት ከተቆጠሩ ግቦች ደግሞ በ17 ዝቅ ብለዋል። የተቆጠሩት ሁሉም 10 ግቦች በተለያዩ ተጫዋቾች የተቆጠሩ ሲሆን የአዳማ ከተማው ከነዓን ማርክነህ 5ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ግብ ፈጣኑ ሲሆን የጅማ አባጅፋር ኤርሚያስ ሀይሉ 90ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠራት ግብ በሳምንቱ ዘግይታ የተቆጠረች ግብ ሆናለች።

ውጤቶችና የደረጃ ሰንጠረዥ

በሳምንቱ ከተደረጉት 8 ጨዋታዎች 5ቱ በአቻ ውጤት ሲጠናቀቁ ቀሪዎቹ ሶስት ጨዋታዎች በመሸናነፍ ተጠናቀዋል። በሳምንቱ የተደረጉት የጨዋታ ውጤቶች እንደሚከተለው በፎቶ አስቀምጠናል።

ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች

የፋሲል ከነማው አጥቂ ሙጂብ ቃሲም በ14 ግቦች የኮከብ ግብ አግቢነቱን ሲመራው ሀብታሙ ገዛኸኝ እና አዲስ ግደይ ከሲዳማ ቡና፣ ብሩክ በየነ ከሀዋሳ ከተማ፣ ፍፁም አለሙ ከባህርዳር ከነማ እና ባየ ገዛኸኝ ከወላይታ ድቻ በእኩል 9 ግብ ይከተላሉ።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዳዊት ታደሰ
Follow:
Hatricksport website writer
Previous Article ሙሉጌታ ምህረት ሀዋሳ ከተማን ተረክቧል !
Next Article ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ17 እና 20 በታች ቡድን አሰልጣኞቹን ይፋ አድርጓል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ቡናናሲዳማ ቡና ድል ሲቀናቸው ጌታነህ ከበደ ማሊያ ያስቀደደው ጨዎታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

Mussie Girmay By Mussie Girmay 9 years ago
Ethiopian Premier League Week 13 recap | Core Points, Results, Scores, and League standing
አሰልጣኝ አዲስ ወርቁ   የሱዳኑ አል ሂላልን ለመቀላቀል ተስማምቷል
ዕድሉ ደረጀ በአሰልጣኝነት ተሹሟል !
የሴካፋ ምድብ ድልድል ይፋ ሆኖአል!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

Š Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?