ከዚህ ቀደም ለአዶላ ወዮ እና ሻኪሶ ከነማ መጫወት የቻለዉ የፊት መስመር አጥቂዉ ቡናማዎቹን መቀላቀሉ ታዉቋል።
በትላንትናው ዕለት ጋናዊ ተከላካይ ወደ ስብስቡ መቀላቀል የቻለዉ ኢትዮጵያ ቡና በዛሬው ዕለት ደግሞ በኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ላይ የውድድሩ ኮከብ ግብ አግቢ እና ኮከብ ተጫዋች የነበረዉን የፊት መስመር ተጫዋቾች አንተነህ ተፈራ በሶስት አመት የኮንትራት ዉል ማስፈረማቸዉን ክለቡ ይፋ አድርጓል።