በሰርቢያዊው አሰልጣኝ ኒኮላ ካቫዞቪች እየተመሩ የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን በአዳማ ከተማ እየከወኑ የሚገኙት ቡናማዎቹ ከግብ ጠባቂዉ አስራት ሚሻሞ በመቀጠል ሁለተኛ ተጫዋች ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።
በዚህም ከዚህ ቀደም ለመቻል ፣ ወልደያ ከተማ ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና ወልቂጤ ከተማ እንዲሁም ከሊጉ ለወረደዉ ክለብ ለገጣፎ ለገዳዲ መጫወት የቻለዉ የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ ሙልጌታ ወ/ጊዮርጊስ በሁለት አመት ውል የመዲናውን ክለብ ኢትዮጵያ ቡና መቀላቀሉ ተረጋግጧል።