By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያ መድን ተከታታይ ድል ሲያሳካ ፤ ባህርዳር ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕናም ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ወልቂጤ ከተማሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባኢትዮጵያ መድህንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችባህርዳር ከተማ

ኢትዮጵያ መድን ተከታታይ ድል ሲያሳካ ፤ ባህርዳር ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕናም ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

ኢትዮጵያ መድን ወልቂጤ ከተማን 3ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

የፕሪሚየር ሊጉ የድሬዳዋ የመጨረሻ ቆይታ በሆነዉ ሀያ ሁለተኛዉ ሳምንት የመጀመሪያ ዕለት ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ወልቂጤ ከተማን 3ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በዋና ዳኛ ሄኖክ አበበ መሪነት በጀመረዉ የዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ሁለቱም ክለቦች ከሚገኙበት የወራጅ ቀጠና ስጋት ለመዉጣት ከሚያደርጉት ጥረት አንፃር ጨዋታዉን እጅግ በጥንቃቄ ለመከዉን ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን ፤ በመርሐግብሩም ገና በመባቻዉ በ4ተኛዉ ደቂቃ ላይ ወልቂጤ ከተማዎች በፋዓድ አብደላ አማካኝነት ሙከራ ቢያደርጉም ኳሷ የግቡን ቋሚ ገጭታ ወጥታለች።

- ማሰታውቂያ -

በተደጋጋሚ ወደ ተጋጣሚ ቡድን የግብ ክልል መድረስ የቻሉት እና በኳስ ቁጥጥሩ ረገድም መጠነኛ ብልጫ የነበራቸዉ ወልቂጤ ከተማዎች እንደነበራቸዉ ብልጫ ግን የግብ ዕድል ለመፍጠር ሲቸገሩ ተስተውሏል። በተቃራኒው በሂደት ወደ ጨዋታዉ መመለስ የቻሉት መድኖች በጄሮም ፍሊፕ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ቢያደርጉም በተመሳሳይ የግቡ ቋሚ ኳሷን መልሷታል።

በድጋሚ ከኋላ ክፍል ሚሊዮን ሰለሞን በረዥሙ የጣለለትን ኳስ ብሩክ ሙሉጌታ ኳሷን ለማግኘት የጣረ ቢሆንም የገር ግን የግብ ዘቡ ፋሪስ በቅልጥፍና ኳሷን ተቆጣጥሯል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ ላይም በ39ነኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ተቆጥሯል ። በዚህም አቡበከር ሳኒ ወደ ሳጥን ያሻገረዉን ኳስ አጥቂዉ ጄሮም ፍሊፕ በግንባሩ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን ኢትዮጵያ መድን መሪ ማድረግ ችሏል።

በሁለተኛዉ አጋማሽ ተሻሽለዉ የተመለሱት ኢትዮጵያ መድኖች በሁለቱም መስመሮች በኩል ጫናን ፈጥረዉ ለመጫወት ሲሞክሩ በተለይ በፊት መስመር ተጫዋቾቹ ጀሮም ፍሊፕ እና አቡበከር ሳኒ አማካኝነት ጥሩ ጥሩ ዕድሎችን መፍጠር ችለዋል።

በ52ተኛዉ ደቂቃ ላይ ብሩክ ሙሉጌታ በጫና የተገኘን ኳስ በቀጥታ ወደ በግብ በመሞክርም እና በተጨማሪም 58ተኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ አቡበከር ሳኒ ጥሩ ሙከራ ቢያደርጉም የግብ ዘቡ ፉሪስ ግን ኳሶቹን አምክኗል። ከመጀመሪያው አጋማሽ አንፃር የተቀዛቀዘ የጨዋታ ጊዜ እያሳለፉ የቀጠሉት ክትፎዎቹ በ80ኛዉ ደቂቃ ላይ ተጨማሪ ግብ አስተናግደዋል። በዚህም አቡበከር ሳኒ ከቡድን አጋሮቹ የተቀበለዉን ኳስ የግል ብቃቱን ተጠቅሞ ያቀበለዉን ኳስ ወገኔ ገዛኸኝ ሁለተኛ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም በዘጠናኛዉ ደቂቃ ላይ በዕለቱ ድንቅ መንቀሳቀስ የቻለዉ አቡበከር ሳኒ አስደናቂ ግብ አስቆጥሮ ጨዋታዉን 3ለ0 በሆነ ዉጤት ኢትዮጵያ መድን ወልቂጤ ከተማን ማሸነፍ ችሏል።

ባህርዳር ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸዉን ያለ ግብ በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል ።

ምሽት አንድ ሰዓት ሲል በርከት ባሉ የደጋፊዎች ድባብ ታጅቦ መከናወን በጀመረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ገና በጊዜ የሀድያዉ ተከላካይ በረከት ቸርነት ጉግሳ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተሰጠዉን የፍፁም ቅጣት ምት ራሱ ቸርነት ጉግሳ ቢመታም ነገር ግን ማስቆጠር ሳይችል ቀርቷል ።

በተመጣጣኝ የጨዋታ እንቅስቃሴ ድንቅ ፉክክርን እያስመለከተን በቀጠለዉ መርሐግብር በ ደቂቃ ላዮ ሀድያዎች ከመስመር በኩል በረከት ያሻገረውን ኳስ የመስመር ተጫዋቹ በየነ ባንጃዉ ሳጥን ዉስጥ በቀጥታ ወደ ግብ ቢሞክርም ኳሷ በግቡ አናት ላይ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በይበልጥ ወደ ግራ ባመዘነ የጨዋታ እንቅስቃሴ ጫና ፈጥረዉ መጫወታቸዉን የቀጠሉት የጣና ሞገዶቹ በ43ተኛዉ ደቂቃ ላይ የመስመር ተከላካዩ ፍራኦል መንግስቱ  ከግራ መስመር በኩል በቀጥታ ወደ ግብ የሞከረዉ ኳስ ወደ ዉጭ ወጥቷል ።

ከዚች የጣና ሞገዶቹ ሙከራ በኋላም ሀድያ ሆሳዕናዎች ከቅጣት ምት በዳዋ ሁቴሳ አማካኝነት በቀጥታ ድንቅ ሙከራ አድርገዉ የነበረ ቢሆንም ኳሷን የግብ ዘቡ ፔፔ ተቆጣጥሯታል። በጨዋታዉ መሐልም አጥቂዉ ሙጅብ ቃሲም የትከሻ ጉዳት አስተናግዶ ተቀይሮ ወጥቷል ።

ከዕረፍት መልስ አባይነህ ፌኖ ከቸርነት ጉግሳ የተቀበለዉን ኳስ ከኋላዉ ለሚገኘዉ ፍቅረሚካኤል አለሙ አቀብሎት የነበረ ሲሆን ተጫዋቹም ኳሷን በቀጥታ ወደ ግብ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን በግቡ አናት ላይ ወጥታለች።

በ71ኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ጠባቂዉ ፔፔ በረዥሙ ሊመታ የነበረዉን ኳስ አጥቂዉ ዳዋ ሁቴሳ ተደርቦ ብሎክ አድርጎበት የነበረ ሲሆን ፤ ከዚያም በኋላ ኳሱን በቀጥታ ወደ ግብ ቢሞክርም ተከላካዮቹ ተረባርበዉ አዉጥተዋል። በ77ተኛዉ ደቂቃ ላይም ከግራ መስመር በኩል የተሻገረዉን የቅጣት ምት ኳስ ተከላካዩ ፍሬዘር ካሳ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

የጨዋታዉ ደቂቃ እየገፋ በሄደ ቁጥር ሁለቱም ክለቦች ጫና ፈጥረዉ በመጫወት አደጋዎችን ለመፍጠር እና ጎሎችን ለመፍጠር ሲያደርጉ የነበረዉ ጥረት ሳይሳካ ቀርቶ ጨዋታዉ ያለ ግብ 0ለ0 በሆነ አቻ ዉጤት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ በአዲስ አባላት መዋቀሩ ይፋ ሆነ ።
Next Article ሀዋሳ ከተማ ሀምበሪቾ ዱራሜን ሲያሸንፍ ፤ በተጠባቂዉ ጨዋታ ፋሲል ከነማ እና አዳማ ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎች

የ2013 የኢትዮጵያ ኘሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ታወቀ

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልምምዳቸውን ቀጥለዋል !
የጨዋታ ዘገባ | የአምስተኛ ሳምንት የመክፈቻ ጨዋታ ግብ ሳይስተናገድበት ተጠናቋል
ካፍ ለጋዜጠኞች ጥሪውን አቅርቧል !
ተወዳጅዋ ባለቀለም ሀትሪክ የስፖርት ጋዜጣችንን የጥቅምት 7 ቀን 2010 ዓ.ም በ ፒ.ዲ.ኤፍ ይመልከቱ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?