By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል
Share
Notification Show More
Latest News
ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….
አትሌቲክስ ዜናዎች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ወላይታ ድቻ ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ ድሬዳዋ ከተማ
የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወልቂጤ ከተማዜናዎች

የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በሊጉ የአምስተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ በቀዳሚነት በተደረገው ጨዋታ ሲዳማ ቡና በእንዳለ ከበደ ብቸኛ ግብ ወልቂጤ ከተማን ረቷል ።

ወልቂጤ ከተማዎች በአራተኛው ሳምንት በሀዋሳ ከተማ በተረቱበት ጨዋታ ላይ በነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አራት ለውጦችን በማድረግ በቴዎድሮስ ሀሙ ፤ ኤፍሬም ዘካሪያስ ፤ አቤል ነጋሽ እና ጌታነህ ከበደ ምትክ ብርሀኑ ቦጋለ ፤ ፋሲል አበባየሁ ፤ ተመስገን በጅሮንድ እና አቡበከር ሳኒን ሲያስገቡ በሲዳማ ቡና በኩል ደግሞ በሳምንቱ በኢትዮጵያ ቡና በተሸነፉበት ጨዋታ በነበረው ምርጥ አስራ አንድ ላይ ምንም ለውጥ ሳያደርጉ ጨዋታውን ጀምረዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ወልቂጤ ከተማዎች የኳስ ቁጥጥር ብልጫ በመውሰድ ለመጫወት ጥረቶችን ሲያርጉ በሲዳማ ቡና በኩል ደግሞ በተለይም ከመስመር ወደ መሀል በሚቀነሱ ኳሶች የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ሞክረዋል ።

- ማሰታውቂያ -

ምንም እንኳን ሁለቱም ክለቦች በየራሳቸው መንገድ የግብ አጋጣሚዎችን ለመፍጠር ጥረቶች ቢያደርጉም ግብ ጠባቂዎችን የፈተኑ ሙከራ ለማድረግ ተቸግረው ቆይተዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ብዙአየሁ ተስፉ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ሆኖ ወደ ግብ የመታው ኳስ ኢላማውን ሳይጠብቅ ቀርቷል ።

በአጋማሹ ግልፅ የጠራ ዕድል በ18ኛው ደቂቃ ላይ የተመለከትን ሲሆን ይገዙ ቦጋለ በሳጥን ውስጥ ሆኖ በረጅም የደረሰውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ኳሱን ከግቡ አናት በላይ ሰዶታል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይም ሌላ ጠንካራ የግብ ሙከራ ሳንመለከት አጋማሹ ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ ሲዳማ ቡና ጫን ብሎ ጨዋታውን የጀመረ ሲሆን በተለይም በመስመሮች በኩል የተጠናከረ የማጥቃት እንቅስቃሴ አድርገዋል ።

በ47ኛው ደቂቃ ላይ መሃሪ መና በግራ መስመር አቅጣጫ ይዞ የገባውን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ ግብ ጠባቂው ሮበርት ኦዶንካራ መልሶታል ። ሮበርት ኦዶንካራ ኳሱን በሚመልስበት ወቅት በቡልቻ ሹራ ጣቱ ላይ በተሰራበት ጥፋት ጨዋታውን መቀጠል ባለመቻሉ በጀማል ጣሰው ተቀይሮ ወጥቷል ።

ወልቂጤ ከተማ የተሻሉ በነበሩቀች ቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ ወደ ፊት ለማድረስ ጥረቶችን ማድረግ ችለዋል ። ነገር ግን ከመሀል የሜዳው ክፍል አልፈው የግብ ዕድል ለመፍጠር በእጅጉ ተቸግረው ነበር ።

በሲዳማ ቡና በኩል ከመሀሪ መና ሙከራ በኋላ ይህ ነው ሊባል የሚችል የግብ ዕድል መፍጠር ያልቻሉ ሲሆን ሶስተኛው የማጥቃት ዞን ላይ ሲገቡ የነበራቸው አፈፃፀም ድክመት ለዚህ መንስኤ ሆኗል ።

በ76ኛው ደቂቃ ላይ ሲዳማ ቡናዎች ያገኙትን የቅጣት ምት ያኩቡ መሀመድ ከግቡ ትይዩ በቀጥታ አክርሮ ወደ ግብ የመታውን ኳስ ጀማል ጣሰው መልሶታል ።

በ79ኛው ደቂቃ ላይም ፍሬው ሰለሞን ከሳጥን ውጨሐ ያደረገው ሙከራ በግብ ጠባቂው ጀማል ጣሰው ተመልሷል ።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ ግን ጎድዊን ኦባጆ ከሙሉቀን አዲሱ በረጅም የተላከለትን ኳስ ተቆጣጥሮ ነፃ ለነበረው እንዳለ ከበደ የቀነሰለትን ኳስ እንዳለ ከመረብ አሳርፎታል ።

ጌታነህ ከበደን ቀይረው በማስገባት ግብ ለማስቆጠር ጥረቶችን ሲያደርጉ በነበረበት ወቅት ግብ ያስተናገዱት ወልቂጤ ከተማዎች በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ ተጭነው ለመጫወት ፍላጎት ቢታይባቸውም አቮኖን የፈተነ የግብ ሙከራ ለማድረግ አልቻሉም ነበር ።

በሲዳማ ቡና በኩል ጨዋታውን በመቆጣጠር ያስቆጠሩትን ግብ አስጠብቀው ለመውጣት ያደረጉት ጥረት ውጤታማ ሆኖ ከጨዋታው ሶስት ነጥብ ይዘው ለመውጣት ችለዋል ።

በስድስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች (ድሬዳዋ ስታድየም) በመጪው ጥቅምት 26(ቅዳሜ) 12:00 ላይ ወልቂጤ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ የሚጫወቱ ሲሆን ጥቅምት 28(ሰኞ) በ9:00 ላይ ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ ይጫወታሉ ።

You Might Also Like

ሁለት ተጫዋቾች የአራት ጨዋታዎች ዕገዳ ሲጣልባቸው ሶስት ክለቦች የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የጨዋታ ዘገባ | ባህርዳር ከተማ ከአራት ዓመታት በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቅዳሜውን ጠቅላላ ጉባኤን አገደ….

የጨዋታ ዘገባ | የስድስተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል

የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛሉ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | አራት ግቦች በተስተናገዱበት ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ የሊጉን መሪ አሸንፈዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
LIVESCOREቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወልቂጤ ከተማዜናዎች

ወልቂጤ ከተማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 3 years ago
የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ ከአስር ድል አልባ ጨዋታዎች በኋላ አሸንፏል
ኢትዮጵያ ቡና ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርሟል
ኮትዲቯር ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማለፏን አረጋግጣለች !
“የሚያኮራ ደጋፊ ባለቤት የሆነውን ኢት.ቡናን ማሰልጠን በመቻሌ ኩራት ይሰማኛል” አሰልጣኝ ዲዲዬ ጎሜዝ ዳሮሳ (ኢት.ቡና)
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?