መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል
ሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወልቂጤ ከተማዜናዎች

የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል

አጋራ
አጋራ

በሊጉ የአምስተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ በቀዳሚነት በተደረገው ጨዋታ ሲዳማ ቡና በእንዳለ ከበደ ብቸኛ ግብ ወልቂጤ ከተማን ረቷል ።

ወልቂጤ ከተማዎች በአራተኛው ሳምንት በሀዋሳ ከተማ በተረቱበት ጨዋታ ላይ በነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ አራት ለውጦችን በማድረግ በቴዎድሮስ ሀሙ ፤ ኤፍሬም ዘካሪያስ ፤ አቤል ነጋሽ እና ጌታነህ ከበደ ምትክ ብርሀኑ ቦጋለ ፤ ፋሲል አበባየሁ ፤ ተመስገን በጅሮንድ እና አቡበከር ሳኒን ሲያስገቡ በሲዳማ ቡና በኩል ደግሞ በሳምንቱ በኢትዮጵያ ቡና በተሸነፉበት ጨዋታ በነበረው ምርጥ አስራ አንድ ላይ ምንም ለውጥ ሳያደርጉ ጨዋታውን ጀምረዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ወልቂጤ ከተማዎች የኳስ ቁጥጥር ብልጫ በመውሰድ ለመጫወት ጥረቶችን ሲያርጉ በሲዳማ ቡና በኩል ደግሞ በተለይም ከመስመር ወደ መሀል በሚቀነሱ ኳሶች የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ሞክረዋል ።

ምንም እንኳን ሁለቱም ክለቦች በየራሳቸው መንገድ የግብ አጋጣሚዎችን ለመፍጠር ጥረቶች ቢያደርጉም ግብ ጠባቂዎችን የፈተኑ ሙከራ ለማድረግ ተቸግረው ቆይተዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ብዙአየሁ ተስፉ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ሆኖ ወደ ግብ የመታው ኳስ ኢላማውን ሳይጠብቅ ቀርቷል ።

በአጋማሹ ግልፅ የጠራ ዕድል በ18ኛው ደቂቃ ላይ የተመለከትን ሲሆን ይገዙ ቦጋለ በሳጥን ውስጥ ሆኖ በረጅም የደረሰውን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ኳሱን ከግቡ አናት በላይ ሰዶታል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይም ሌላ ጠንካራ የግብ ሙከራ ሳንመለከት አጋማሹ ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ ሲዳማ ቡና ጫን ብሎ ጨዋታውን የጀመረ ሲሆን በተለይም በመስመሮች በኩል የተጠናከረ የማጥቃት እንቅስቃሴ አድርገዋል ።

በ47ኛው ደቂቃ ላይ መሃሪ መና በግራ መስመር አቅጣጫ ይዞ የገባውን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ ግብ ጠባቂው ሮበርት ኦዶንካራ መልሶታል ። ሮበርት ኦዶንካራ ኳሱን በሚመልስበት ወቅት በቡልቻ ሹራ ጣቱ ላይ በተሰራበት ጥፋት ጨዋታውን መቀጠል ባለመቻሉ በጀማል ጣሰው ተቀይሮ ወጥቷል ።

ወልቂጤ ከተማ የተሻሉ በነበሩቀች ቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ ወደ ፊት ለማድረስ ጥረቶችን ማድረግ ችለዋል ። ነገር ግን ከመሀል የሜዳው ክፍል አልፈው የግብ ዕድል ለመፍጠር በእጅጉ ተቸግረው ነበር ።

በሲዳማ ቡና በኩል ከመሀሪ መና ሙከራ በኋላ ይህ ነው ሊባል የሚችል የግብ ዕድል መፍጠር ያልቻሉ ሲሆን ሶስተኛው የማጥቃት ዞን ላይ ሲገቡ የነበራቸው አፈፃፀም ድክመት ለዚህ መንስኤ ሆኗል ።

በ76ኛው ደቂቃ ላይ ሲዳማ ቡናዎች ያገኙትን የቅጣት ምት ያኩቡ መሀመድ ከግቡ ትይዩ በቀጥታ አክርሮ ወደ ግብ የመታውን ኳስ ጀማል ጣሰው መልሶታል ።

በ79ኛው ደቂቃ ላይም ፍሬው ሰለሞን ከሳጥን ውጨሐ ያደረገው ሙከራ በግብ ጠባቂው ጀማል ጣሰው ተመልሷል ።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ ግን ጎድዊን ኦባጆ ከሙሉቀን አዲሱ በረጅም የተላከለትን ኳስ ተቆጣጥሮ ነፃ ለነበረው እንዳለ ከበደ የቀነሰለትን ኳስ እንዳለ ከመረብ አሳርፎታል ።

ጌታነህ ከበደን ቀይረው በማስገባት ግብ ለማስቆጠር ጥረቶችን ሲያደርጉ በነበረበት ወቅት ግብ ያስተናገዱት ወልቂጤ ከተማዎች በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ ተጭነው ለመጫወት ፍላጎት ቢታይባቸውም አቮኖን የፈተነ የግብ ሙከራ ለማድረግ አልቻሉም ነበር ።

በሲዳማ ቡና በኩል ጨዋታውን በመቆጣጠር ያስቆጠሩትን ግብ አስጠብቀው ለመውጣት ያደረጉት ጥረት ውጤታማ ሆኖ ከጨዋታው ሶስት ነጥብ ይዘው ለመውጣት ችለዋል ።

በስድስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች (ድሬዳዋ ስታድየም) በመጪው ጥቅምት 26(ቅዳሜ) 12:00 ላይ ወልቂጤ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ የሚጫወቱ ሲሆን ጥቅምት 28(ሰኞ) በ9:00 ላይ ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ ይጫወታሉ ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...