By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ በአዲስ አባላት መዋቀሩ ይፋ ሆነ ።
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንዜናዎች

የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ በአዲስ አባላት መዋቀሩ ይፋ ሆነ ።

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
Share
SHARE

አዲስ የተሻሻለው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ደንብ ለፊፋ ተልኮ እንዲፀድቅ በመደረጉ ብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ በአዲስ መልክ እንዲዋቀርና ከዚህ ቀደም በኢንተርናሽናል ዳኝነት ሲያገለግሉ የቆዩ ግለሰቦች በአመራርነት እንዲሰሩ መምረጡ ተሰማ።

ኮሚቴው በአዲስ መልክ እንዲዋቀር መነሻ የሆነው ጥቅምት 19/2016 በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የፀደቀው የተሻሻለው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መተዳደርያ ደንብ ሲሆን በደንቡ አንቀፅ 46 (ቁጥር 2) ላይ ቋሚ ኮሚቴዎች የሚቋቋሙበት ሁኔታ ሲገልፅ “ከብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ በቀር የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይም ምክትል ሰብሳቢ ሆኖ መስራት ይችላል። ” ይላል። የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴን አወቃቀር እና አሠራር ገለልተኛ ለማድረግም አባላቱ ከሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ውጪ እንደሚሆኑ በደንቡ ላይ ተቀምጧል። ይህን ተከትሎ የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ሙሉ ለሙሉ በአዲስ መልክ እንዲዋቀር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ትናንት ባደረገው ስብሰባ ውሳኔ ወስኗል ሲል ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ ሰብሳቢ በነበሩት ኮሚሽነር ሸረፋ ደሌቾ ይመራ የነበረውና ኢንስትራክተር ልዑል ሰገድ በጋሻው ፣ ኮሚሽነር ሰላሙ በቀለ፣ ኢንተርናሽናል ረዳት አርቢትር በላቸው ይታየውና ኢንተርናሽና አርቢትር አዲስ ነጋሽ የተካቱበት ነባሩ ኮሚቴ ከትላንት ምሽት ጀምሮ በይፋ መሰናበቱን የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

ዛሬ ስራውን በይፋ የጀመረው አዱሱ የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴን ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ ሸዋንግዛው ተባባል በሰብሳቢነት ሲመራው ኢንተርናሽናል አርቢትር የነበረችው ሊዲያ ታፈሰ በምክትል ሰብሳቢነት እንዲሁም ኢንተርናሽናል ረዳት አርቢትር የነበረው ክንዴ ሙሴ፣ ኢንተርናሽናል አርቢትር ለማ ንጉሴና ኢንተርናሽናል ረዳት አርቢትር ክንፈ ይልማ በአባልነት መካተታቸው ታውቋል። ከነባር ኮሚቴው ድሬዳዋ ላይ ሆነው የዳኛ ምደባ ላይ ሲሰሩ የነበሩት ኮሚሽነር ሰላሙ በቀለ ትላንት ከሆቴላቸው የወጡ ሲሆን በቦታው የአዲሱ ኮሚቴ ምክትል የሆየችው ሊዲያ ድሬዳዋ ከተማ በመገኘት የዛሬውን ምደባ ከሌሎች አካላት ጋር ሆና ማከናወኗ ታውቋል።

- ማሰታውቂያ -

የሁለቱ ኮሚቴዎች ፈጣን ልውውጥ በርካቶችን ያነጋገረ ሲሆን በተለይ ሊጠናቀቅ 9 ጨዋታ በቀረው የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ለዋንጫና ላለመውረድ የሚደረገው ትንቅንቅ ሊይ የሚመደቡት ዳኞች ወሳኝ በመሆናቸው በኮሚሽነር ሸረፋ የሚመራው ኮሚቴ እንደጀመረው ቢጨርስ መልካም ነበር የሚሉ ወገኖችም ተበራክተዋል። የክለቦችም ይሁን የተለያዩ ወገኖች ፍላጎቶች በይበልጥ በሚጧጧፍበት የመጨረሻዎቹ ሳምንታት ጨዋታዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚጠይቁ በመግለጽ ለምን አሁን ሆነ የሚሉ ወገኖች ስጋታቸውን ያሰማሉ።

ከ23ኛው ሳምንት ጀምሮ ወደ ሀዋሳ የሚዞረው ፕሪሚየር ሊጉ ለጥሎ ማለፉ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ሲባል ለቀናቶች መቋረጡ የማይቀር መሆኑን የሚናገሩት ወገኖች ለነባሩ ኮሚቴ አመስግኖና ሽኝት አድርጎ የተወሰነም ቢሆን የልምድ ልውውጥ እንዲኖር አለመደረጉ አነጋጋሪ ሆኗል።

አዲሱ ኮሚቴ ሃላፊነቱን እስከወሰደ ድረስ የቀጣዮቹ የፕሪሚየር ሊግ የዋንጫና ላለመውረድ በሚደረገው ፍልሚያ በከፍተኛ ሊግ ደግሞ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ለማደግና ወደ አንደኛ ሊግ ላለመውረድ በሚኖረው ፍጥጫ ላይ ተገቢ የሆኑ አርቢትሮችን በመመደብና ውጫዊ ጫና ባለመስማት ተገቢ የሆነ አመራር እንደሚሰጡ አደራ የተጣለባቸው ሆኗል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀያ አንደኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ!
Next Article ኢትዮጵያ መድን ተከታታይ ድል ሲያሳካ ፤ ባህርዳር ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕናም ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን በመርታት ወደ ሊጉ መሪነት ተመልሷል

hatricksport team By hatricksport team 9 years ago
ዳዊት ተፈራ ወደ ነገሌ አርሲ አመራ !!
ኢትዮጵያ ቡና በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ የመጀመሪያ ጨዋታዉን ዛሬ ያደርጋል !!
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ 21ኛ ሳምንት ጨዋታ ውጤት እና የደረጃ ሰንጠረዥ
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በመጀመሪያ ዙር የነበሩ ክስተቶች (ክፍል አንድ)
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?