*..ኡመድ ኡኩሪም ቀጣዩ ፈራሚ…?
የአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ጅማ አባጅፋር ኮከቦችን መሰብሰቡንና የተሻለ ቡድን የመገንባት ጥረቱን ገፍቶበታል።
በ2003 ኢትዮዽያ ቡናን ለዋንጫ ካበቁት ኮከቦች መሃል የሚገኙት ዳዊት እስጢፋኖስና መስዑድ መሀመድን እንዲሁም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር በርካታ ድሎችን የተቀዳጀውን ሳላህዲን ሰይድን ያስፈረሙት ጅማ አባጅፋሮች አሁን ደግሞ የቀድሞ የፈረሰኞቹ ኮከብ ኡመድ ኡኩሪን ለማስፈረም ተስማምተዋል።
ተጨዋቹ “በሀድያ ሆሳህና የደረሰብኝ መንገላታትን አልፈልግም የተስማማንበት ክፍያ ይሰጠኝ” በማለቱ ውሉን የማጸደቁ ሂደት ዘገየ እንጂ በሁሉም መልኩ ከክለቡ ጋር መስማማቱ ታውቋል።
- ማሰታውቂያ -
ጅማ አባጅፋር ከፋይናንስ አንጻር ያለበትን ክፍተት የሚደፍን ከሆነ በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ስር ጠንካራና ለዋንጫ የሚፎካከር ቡድን እንደሚገነባ ይታመናል።