መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ ኢትዮጵያ መድን እና ሀዋሳ ከተማ አቻ ተለያይተዋል
ሀዋሳ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ መድህንዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

ኢትዮጵያ መድን እና ሀዋሳ ከተማ አቻ ተለያይተዋል

አጋራ
አጋራ

 

በአስረኛዉ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ቀን ሁለተኛ ጨዋታ የተገናኙት ኢትዮጵያ መድን እና ሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸዉን 0ለ0 በሆነ አቻ ዉጤት አጠናቀዋል።

የሊጉን መሪነታቸውን በዘጠነኛው ሳምንት ለመዲናዉ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስ አሳልፈዉ የሰጡት ኢትዮጵያ መድኖች የምሽቱን ጨዋታ በድል ተወጥተዉ ቢያንስ ቅዲስ ጊዮርጊስ እስከሚጫወት ድረስ ወደ መሪነት ይመለሳሉ ተብሎ ተጠብቆ የነበረ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል። እስከ አሁን ድረስ በሊጉ በቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ ባህርዳር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ብቻ ሽንፈትን ያስተናገዱት መድኖች ከጨዋታ ጨዋታ ራሳቸዉን በማሻሻል እና በሂደት እንደ ቡድን በጥንካሬ በመምጣት በደረጃ ሰንጠሰዡ አናት ላይ ከሚገኙ ክለቦች ተርታ ራሳቸዉን ማስቀመጣቸዉም አስደናቂ ጉዞ ሆኖ ተመዝግቦላቸዋል።

በተቃራኒው ወጥ የሆነ አቋም ከጨዋታ ጨዋታ ለማስመልከት እየተቸገሩ የመመገኙት ሀዋሳ ከተማዎች በቅርብ ሳምንታት እንደ ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና የመሳሰሉ ክለቦችን መርታት ችለዉ የነበረ ቢሆንም በዘጠነኛዉ ሳምንት የሊጉ መርሐግብር ግን በቅዱስ ጊዮርጊስ ያልተጠበቀ የሶስት ለዜሮ ሽንፈት ማስተናገዳቸዉ ይታወሳል። በዚህም ከሽነፈት ለማገገም ወሳኝነቱ የላቀ በነበረዉ የምሽቱ ጨዋታ ከኢትዮጵያ መድን ጋር የጥብ ተጋርተዉ ወጥተዋል።

ዉጤቱን ተከትሎም የገብረ መድህን ሀይሌዉ ኢትዮጵያ መድን በአንድ ነጥብ በልጦ መሪነቱ መረከብ ችሏል። በቀጣይ የሊጉ የአስራ አንደኛ ሳምንት መርሐግብርም ኢትዮጵያ መድን ከወልቂጤ ጋር ሲገናኙ ሀዋሳ ከተማ ደግሞ ከመቻል ጋር የሚጫወቱም ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...