“ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ጥያቄ አላቀረበችም”
“የሚናፈሰዉ ወሬ ሀሰት ነዉ ” አቶ ባህሩ ጥላሁን
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ብሔራዊ ቡድኑ ወደ ሀገር ቤት ተመልሶ የሚጫወትበትን መንገድ በማፈላለግ ላይ እንጅ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት በሚል ምንም አይነት ያቀረበዉ ጥያቄ የለም።
ፌደሬሽኑ ሌሎች ስራዎች አሉበት በተለይ ዋልያዎቹ በቀጣይ በሜዳቸዉ እንዲጫወቱ ነዉ እየሰራን የምንገኘዉ እንጅ በፍፁም የአፍረካ ዋንጫ ለማዘጋጀት ጥያቄ አላቀረብንም በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰዉ ወሬ ሀሰት ነዉ ሲሉ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ዋና ፀሀፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ከትርታ ራዲዮ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ተናግረዋል።