By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ጣፋጭ ድል አስመዝግበዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግፋሲል ከነማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ጣፋጭ ድል አስመዝግበዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

አስገራሚ የጨዋታ እንቅስቃሴ በታየበት የምሽቱ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ሀድያ ሆሳዕናን ከኋላ ተነስቶ 2 – 1 አሸንፏል ። በተለይም በሁለተኛው አጋማሽ የነበረው የእርስ በርስ የሜዳ ላይ ፉክክር ብዙ መልኮች የነበሩት ነው ።

በጨዋታው በፋሲል ከነማ በኩል ሀዋሳ ከተማን በረቱበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ ምርጥ አስራአንድ ላይ ለውጥ ሳያደርጉ ሲገቡ በሀድያ ሆሳዕና በኩል ደግሞ በሳምንቱ ከለገጣፎ ለገዳዲ አቻ በተለያዩበት ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ ሁለት ለውጦችን በማድረግ በፀጋዬ ብርሀኑ እና ራምኬል ሎክ ምትክ ዳግም ንጉሴን እና ተመስገን ብርሀኑን ተክተው ወደ ሜዳ ገብተዋል ።


በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ሀድያ ሆሳዕናዎች በተሻለ የበላይነት መንቀሳቀስ የቻሉበት ነበር ። ጥሩ ጥሩ የግብ ዕድሎችን ማግኘት ቢችሉም ሳይጠቀሙባው ለረጅም ደቂቃዎች ቆይተዋል ።

በ20ኛው ደቂቃ ላየ ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን ከርቀት አክርሮ ወደ ግብ የመታው ኳስ በግቡ ቋሚ ተመልሶ ወቷል ።

- ማሰታውቂያ -

በፋሲል ከነማ በኩል ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ከመድረስ እና የግብ ዕድሎችን ከመፍጠር አንፃር ይህ ነው ሊባል የሚችል የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ለማሳየት ተቸግረው ቆይተዋል ።

በጨዋታው 32ኛው ደቂቃ ላይ የስታድየሙ መብራት መጥፋቱም ተከትሎ ጨዋታው ለተወሰኑ ደቂቃዎች እንዲቋረጥም አድርጓል ።

የስታድየሙ መብራት ተመልሶ ጨዋታው በቀጠለበት አጋጣሚ አፄዎቹ ቀደም ብሎ ከነበራቸው የተሻለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴን ለመሳየት ችለውም ነበር ። በዚህም በ34ኛው ደቂቃ ላይ አጥቂው ኦሴ ማውሊ ከመስመር ተሻግሮለት በግንባር የገጨው ኳስ በፔፔ ሰይዶ ግብ ከመሆን ድኗል ።

አጋማሹ መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ ግን ሀድያ ሆሳዕናዎች መሪ የሆኑበትን ግብ አግኝተዋል ። የሀድያ ሆሳዕናው አጥቂ ባዬ ገዛኸኝ በሳጥን ውስጥ ሆኖ ያገኘውን ኳስ ለመጠቀም ሲሞክር በሳማኪ ሚካኤል ጥፋት ተሰርቶበት የፍፁም ቅጣት ምት አግኝተዋል ። የፍፁም ቅጣት ምቱንም ራሱ ባዬ ገዛኸኝ ከመረብ አሳርፎታል ።

ሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እጅግ በርካታ ትዕይንቶች የተስተናገዱበት ነበር ። በአጋማሹ ፋሲል ከነማዎች ይበልጥ የተሻለ ሆነው ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል መድረስ ችለው ነበር ።

በተለይም ልክ አጋማሹ በተጀመረ ሰከንዶች ውስጥ አለምብርሀን ይግዛው ከቀኝ መስመር ያሻገረውን ኳስ ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ በግንባር ገጭቶ ለማስቆጠር ያደረገው ድንቅ ሙከራ በፔፔ ሰይዶ ግብ ከመሆን ድኗል ።

በ51ኛው ደቂቃ ላይ ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን ከሳጥን ውጪ ያደረገው እና በሳማኪ ሚካኤል የተመለሰው ሙከራ በአጋማሹ ለሀድያ ሆሳዕና የመጀመሪያም የመጨረሻም የግብ ሙከራ ሆኗል ።

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ዱላ ሙላተለ ከታፈሰ ሰለሞን የደረሰውን ግሩም ኳስ ወደ ግብ መሞከር ቢችልም በግብ ጠባቂው ተመልሷል ።

በአፄዎቹ በኩል በተለይም የሽመክት ጉግሳ እና የሱራፌል ዳኛቸው ተቀይረው ወደ ሜዳ መግባታቸው የተሻሉ የግብ ዕድሎችን ከመፍጠር አንፃር ግልፅ አጋጣሚዎች ማግኘት ችለዋል ።

በዚህም ከሁለቱ ተጫዋቾች እግር በተነሱ ኳሶቸሰ ግቦች ተቆጥረዋል ።

ሱራፌል ዳኛቸው ተቀይሮ በገባበት አጋጣሚ በመጀመሪያ የኳስ ንክኪው ከቅጣት ምት በቀጥታ ወደ ግብ የመታው ኳስ በግብ ጠባቂው ተመልሷል ።

በ74ኛው ደቂቃ ላይም ኦሴ ማውሊ ከሽመክት ጉግሳ የደረሰውን አስደናቂ ኳስ ከመረብ በማሳረፍ የጨዋታውን ውጤት ወደ 1 – 1 ቀይሯል ።

ከዚህ ግብ መቆጠር በኋላ በተለይም አፄዎቹ ተጨማሪ ግብ አስቆጥረው ለማሸነፍ በሀድያ ሆሳዕና በኩል ደግሞ ውጤቱን አስጠብቀው ለመውጣት ጥረቶች የተደረጉበት እና ከጨዋታ ላይ እንቅስቃሴ ባለፈም የተጫዋቾች የእርስ በርስ ሹክቻ በተደጋጋሚ የታየበት ነበር ።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በተጨማሪ ደቂቃዎች ላይም አፄዎቹ ከመመራት ተነስተው ድል ያደረጉበትን ግብ አስቆጥረዋል ።

ሱራፌል ዳኛቸው ከቅጣት ምት ያሻገረውን ኳስ ሽመክት ጉግሳ በግንባር ገጭቶት በፔፔ ሰይዶ ሲመለስ በቅርበት የነበረው ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

በመጨረሻም አፄዎቹ በ2 – 1 ድል ሶስት ነጥቦችን ማሳካት ችለዋል ።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የጦና ንቦቹ በተከታታይ ድል የአዳማ ቆይታቸውን አገባደዋል !!
Next Article የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በተከታታይ ጨዋታዎች ነጥብ ጥለዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግፋሲል ከነማ

አፄዎቹ ዝግጅት የሚጀምሩበት ቀን ታውቋል !!

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 3 years ago
የ2012 ዓ.ም ከ20 ዓመት በታች ወጣቶች ኘሪሚየር ሊግ 1ኛ ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ታውቋል
አሰልጣኝ እንድርያስ ብርሃኑ የኢትዮጵያ ከ17ዓመት በታች ወንዶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
​የጋዜጠኛ ኢብራሂም  ሻፊ ግብዐተ መሬት ተፈፀመ፡፡
የጨዋታ ዘገባ | ፈረሰኞቹ ዓመቱን በድል ጀምረዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?