By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ወልቂጤ ከተማ እና ሻሸመኔ ከተማ አቻ ሲለያዩ ፤ ኢትዮጵያ መድንም ከአስራ ሁለት ሳምንታት በኋላ ማሸነፍ ችሏል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
መቻልሻሸመኔ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችወልቂጤ ከተማየጨዋታ ዘገባኢትዮጵያ መድህን

ወልቂጤ ከተማ እና ሻሸመኔ ከተማ አቻ ሲለያዩ ፤ ኢትዮጵያ መድንም ከአስራ ሁለት ሳምንታት በኋላ ማሸነፍ ችሏል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ አንደኛዉ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሶስተኛ ዕለት የመጀመሪያ ጨዋታ በወራጅ ቀጠናዉ ዞን ላይ የሚገኙት ወልቂጤ ከተማ እና ሻሸመኔ ከተማ ጨዋታቸውን ያለ ገብ በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል ።

በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ መሪነት ቀን 10:00 ሰዓት ሲል በጀመረዉ እና ከወራጅ ቀጠናዉ ዞን ለመሸሽ ወሳኝ በነበረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከጨዋታዉ መባቻ አንስቶ ደካማ የሚባል እንቅስቃሴ የተመለከትንበት ሲሆን ፤ እንቅስቃሴዉም የመጀመሪያ ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ለማስመልከት 22 ደቂቃዎችን ያስጠበቀ ሲሆን ፤ በተጠቀሰው ደቂቃም ወልቂጤ ከተማዎች ከቀኝ መስመር በኩል ከተገኘ ቅጣት ምት በጋዲሳ መብራቴ አማካኝነት ድንቅ ለግብ የቀረበ ሙከራ አድርገዋል።

ከዚች ሙከራ በቀር በአጋማሹ ይህ ነዉ የሚባል ተጠቃሽ አደገኛ ሙከራን ማስመልከት ያልቻሉት ሁለቱም ክቦች እጅጉኑ ቀዝቃዛ የነበረዉን የመጀመሪያ አጋማሽ ያለ ግብ በአቻ ዉጤት አገባደዉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍሉ ያመሩ ሲሆን ፤ ከዕረፍት መልስም እንደመጀመሪያው አጋማሽ ሁሉ ጨዋታዉ በቀዝቃዛ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የቀጠለ ሲሆን ከነበሩ አንድ ሁለት ተጠቃሽ ሙከራዎች መካከልም በ56ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር በኩል ጋዲሳ መብራቴ ለሳምሶን ጥላሁን ድንቅ ኳስ አቀብሎት ተጫዋቹ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ ኬን ሰይዲ ኳሷን ግብ ከመሆን እንደምንም አምክኗል።

- ማሰታውቂያ -

የጨዋታዉ ደቂቃዎች እየገፉ በሄዱ ቁጥሩ ይበልጥኑ እየተቀዛቀዘ በቀጠለዉ ጨዋታ ሻሸመኔ ከተማዎች በስንታየሁ መንግሥቱ አማካኝነት አንድ ሁለት ለግብ የቀረቡ ሙከራዎችን አድርገዉ ፤ በተመሳሳይ ክትፎዎቹም በተመስገን አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ቢያደርጉም ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ጨዋታዉ 0ለ0 በሆነ አቻ ዉጤት ተጠናቋል።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ከመመራት ተነስቶ መቻልን 2ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

በሁለት ፅንፍ በኩል በሚገኙት ክለቦች መካከል ምሽት አንድ ሰዓት ሲል በጀመረዉ ጨዋታ ገና በመባቻዉ መቻል ግብ አስቆጥረዋል ። በዚህም ዮዳሄ ዳዊት ከግራ መስመር በኩል ያሻገረዉን ኳስ ምንይሉ ወንድሙ ሲጨርፈዉ ያገኘወለ ሽመልስ በቀለ ወደ ጎልነት ቀይሮ ክለቡን ገና በ1ኛዉ ደቂቃ መሪ አድርጓል።

ገና በጨዋታዉ መጀመሪያ ደቂቃ ላይ ግብ ከተቆጠረባቸው በኋላ የአቻነት ግብ ለማግኘት በቶሎ መንቀሳቀስ የቻሉት መድኖች ዉጥናቸዉ ሰምሮ በ10ኛዉ ደቂቃ ላይ አቻ መሆን ችለዋል ። በዚህም በመልሶ ማጥቃት የተገኘዉን ኳስ ጄሮም ፍሊፕ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ ግብ ጠባቂዉ ኳሷን ሲመለስ በቅርበት ያገኛት አብዱልከሪም መሐመድ ግብ አስቆጥሮ ክለቡን አቻ አድርጓል።

ጨዋታዉ ገና በጊዜ ሁለት ጎሎች ከተቆጠሩበት በኋላ በመጠኑ እየተቀዛቀዘ ሂዶ ግማሽ ሰዓታ ያክል ሲያስቆጥር ሁለቱም ክቦች የተጠራ የግብ ዕድል ለመፍጠርም በብዙ ሲቸገሩ ተስተውሏል። ሁለቱም በኳስ ቁጥጥሩ የበላይ ለመሆን ከሚያደርጉት ፉክክር ባሻገር በአጋማሹ መገባደጃ ወቅት መቻል በከንዓን ማርክነህ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ አድርገዉ ነበር ፤ በዚህም ተጫዋቹ ከዮሐንስ መንግስቱ የተቀበለውን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ቢልክም ኳሷ ለጥቂት ወጥታለች። ከዚያ ውጭ አቤል ነጋሽም ድንቅ የሚባል ሙከራ ማድረግ ችሎ የነበረ ሲሆን ፤ መድኖችም በወገኔ ገዛኸኝ አማካኝነት ለግብ የቀረበ ሙከራ ማድረግ ችለዉ ነበር ።

ከዕረፍት መልስ ሁለቱም ክለቦች የሜዳዉን የመሐል ክፍል ላይ ብልጫ ለመዉሰድ ከሚደረግ ፉክክር በዘለለ ያን ያህል ተጠቃሽ ሙከራዎች ሳይደረጉበት ሁለተኛዉ አጋማሽም ዘለግ ላለ ጊዜ ቀጥሏል ። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ የምሽቱ መርሐግብርም በ75ተኛዉ ደቂቃ ላይ መድኖች ግብ ለቆጠርባቸዉ ከጫፍ ደርሰዉ በተከላካዩ ሚሊዮን ሰለሞን ጥረት የመቻሎች ሙከራ ከሽፏል።

በጨዋታዉ መገባደጃ ወቅት ከንዓን ማርክነህ በሚሊዮን ሰለሞን ጥፋት ተሰርቶበታል በሚል እና ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ በላይ ታደሰ ባልሰጡት ፍፁም ቅጣት ምት ከነበረዉ አከራካሪ ሁነት በኋላ መደበኛዉ ዘጠና ደቂቃ ተገባዶ በተጨመረዉ ሰባት ደቂቃ ላይ ኢትዮጵያ መድን በአብዱልከሪም መሐመድ አማካኝነት ሁለተኛ ግብ አስቆጥረዉ ጨዋታዉ በኢትዮጵያ መድን 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ፋሲል ከነማ ከሀምበሪቾ ዱራሜ ጋር አቻ ሲለያይ ፤ ባህርዳር ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስም መርሐግብራቸዉን በተመሳሳይ በአቻ ዉጤት ፈፅመዋል !!
Next Article በሳምንቱ የመጨረሻ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወሳኝ ድል ሲያሳካ ፤ አዳማ ከተማም ኢትዮጵያ ቡናን አሸንፏል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችደደቢት

ደደቢት የክረምቱ አምስተኛ ዝውውሩን አጠናቀቀ

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 6 years ago
የጨዋታ ሪፖርት|ቅዱስ ጊዮርጊስ መሪነቱን ያጠናከረበትን ድል ጅማ ላይ ተቀዳጅቷል 
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ ወደ ሶዶ ተጉዞ ጣፋጭ ሶስት ነጥብ አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ፕሪሜየር ለግ 11ኛ ሳምንት /LIVESCORE/
የጨዋታ ዘገባ | ሳቢ ያልነበረው የመከላከያ እና የጅማ አባጅፋር ጨዋታ ያለ ግብ ተጠናቋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?