By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: በሳምንቱ የመጨረሻ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወሳኝ ድል ሲያሳካ ፤ አዳማ ከተማም ኢትዮጵያ ቡናን አሸንፏል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
ዜናዎች ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችሲዳማ ቡናአዳማ ከተማሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡና

በሳምንቱ የመጨረሻ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወሳኝ ድል ሲያሳካ ፤ አዳማ ከተማም ኢትዮጵያ ቡናን አሸንፏል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ አንደኛዉ ሳምንት የሊጉ መርሐግብር የመጨረሻ ዕለት ጨዋታ ቀን 10:00 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ሀድያ ሆሳዕናን አሸንፏል ።

የነብሮቹን የጨዋታ የበላይነት እያስመለከተ በጀመረዉ መርሐግብር ገና በመባቻዉ በ9ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሀድያዎች መሪ መሆን ችለዋል ። በዚህም ባለ ግራ ዕግሩ ሳሙኤል ዮሐንስ ከርቀት ገና በጊዜ ድንቅ ግብ አስቆጥሮ ጨዋታውን መምራት ጀምረዋል። ገና በጊዜ ግብ የተቆጠረባቸዉ እና በእንቅስቃሴም አጀማመሩ ላይ ብልጫ የተወሰደባቸዉ ሲዳማ ቡናዎች በሂደት ወደ ጨዋታዉ ገብተዉ በቡልቻ ሹራ አማካኝነት ከግራ መስመር በኩል ድንቅ የሚባል ለግብ የቀረበ ሙከራ ማድረግ ችለዋል።

በተደጋጋሚ ጫና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉት ሲዳማዎች አጋማሹ ሳይገባደድ የአቻነት ግብ አግኝተዋል ። በዚህም ቡልቻ ሹራ ወደ መስመር ተጠግቶ የተገኘዉን የቅጣት ምት ኳስ ሲያሻማ ራሱ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን አቻ አድርጓል። የአቻነት ግብ ከተቆጠረ በኋላ ተመጣጣኝ የጨዋታ ፉክክር እያስመለከተን በቀጠለዉ ጨዋታ ተጨማሪ ግብ ሳይቆጠር አጋማሹ ተገባዷል።

- ማሰታውቂያ -

በሁለተኛው አጋማሽም ሁለቱም ክለቦች እንደ መጀመሪያዉ አጋማሽ ሁሉ የጨዋታዉ የመሐል ሜዳ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ከመጣር በዘለለ በሙከራ ረገድ ደካማ ሆነዉ የቀጠሉ ሲሆን ፤ በ70ኛዉ ደቂቃ ላይ ግን በሂደት ብልጫ መዉሰድ የቻሉት ሲዳማዎች ጨዋታውን መምራት ጀምረዋል ። በዚህም ቡልቻ ሹራ ከማይክል ኪፕሩል ተቀብሎ ለራሱ ለተጫዋቹ ያመቻቸለትን ኳስ በግሩም ሁኔታ ወደ ግብነት በመቀየር ሲዳማን ከመመራት ወደ መሪነት አሸጋግሯል።

በእጃቸዉ የነበረዉን ወርቃማ እድል አሳልፈዉ የሰጡት ሀድያ ሆሳዕናዎች በርከት ያሉ የማጥቃት ባህሪ ያላቸዉን  ተጫዋቾች ቀይረዉ ወደ ሜዳ ቢያስገቡም ዉጥናቸዉ ሰምሮ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ጨዋታዉ በሲዳማ ቡና 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በዕሁለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና በአዳማ ከተማ የ2ለ1 ሽንፍት አስተናግዷል ።

ምሽት 1:00 ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ቢኒያም ወርቅአገኘዉ መሪነት በጀመረው ተጠባቂ ጨዋታ በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ሁለቱም ክለበች ተመጣጣኝ በሚባል የሜዳ ላይ ፉክክር ማራኪ የጨዋታ እንቅስቃሴ ሲያስመለክቱን የነበረ ሲሆን ፤ ሙከራ ለማድረግ ግን 24 ደቂቃዎችን መጠበቅ ግድ ብሎ ነበር ። በዚህም ቡናማዎቹ ከቀኝ መስመር በኩል በአብዱልከሪም ወርቁ አማካኝነት ያሻገሩትን ኳስ አጥቂዉ አንተነህ ተፈራ በጭንቅላቱ ወደ ግብ ቢልክም ኳሷን ግብ ጠባቂዉ ሰይድ ተቆጣጥሯል።

ከዚች ሙከራ ከሁለት ደቂቃዎች በኋላም አዳማ ከተማዎች ጥሩ ዕድል መፍጠር ችለዉ ነበር ፤ በዚህም ከግራ መስመር በኩል ቢኒያም አይተን ያቀበለዉን ኳስ ዮሴፍ ታረቀኝ ወደ ግብነት ቀየረዉ ተብሎ ቢታሰብም የግብ ዘቡ በረከት ኳሷን እንደምይም አክሽፏታል። በ29ነኛዉ ደቂቃ ላይ ግን በጥሩ ቅብብል ቡናማዎቹ ሳጥን ውስጥ ከደረሱ በኋላ ሱራፌል ዐወል አማኑኤል አድማሱ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተገኘዉን ፍፁም ቅጣት ምት መስፍን ታፈሰ ቢመታዉም ኳሷን አምክኗታል።

በ31ኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ በመልሶ ማጥቃት የቡናማዎቹ ሳጥን ውስጥ የደረሱት አዳማዎች ጀሚል ያዕቆብ ወደ ግብ ሞክሯት የተመለሰችዉን ኳስ ዮሴፍ ከመረቡ ጋር ቀላቅሎ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ከዕረፍት መልስ የአቻነት ግብ ለማግኘት ጫና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉት ቡናማዎቹ በ50ኛዉ ደቂቃ ላይ አብዱልከሪም ወርቁ ያቀበለዉን ኳስ አማኑኤል አድማሱ በቀጥታ ወደ ግብ ቢሞክርም ግብ ጠባቂዉ ሰይድ ሀብታሙ ኳሷን ተቆጣጥሯል።

የመሪነት ግብ ካስቆጠሩ በኋላ በይበልጥ ወደ ራሳቸዉ የግብ ክልል አዘንብለዉ በመጫወት ጥንቃቄን መርጠዉ አልፎ አልፎም በመልሶ ማጥቃት አደጋን ለመፍጠር ሲጥሩ የነበሩት አዳማ ከተማዎች በ63ተኛዉ ደቂቃ ከቅጣት ምት በሱራፌል ምክንያት ድንቅ ሙከራን ቢያደርጉም ኳሷ የገቡን አግዳሚ ነክታ ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በተደጋጋሚ ጨና ፈጥረዉ በመጫወት ዕድሎችን ለማግኘት ይጥሩ የነበሩት ቡናማዎቹ መነሻቸዉን ከአብዱልከሪም ባደረጉ ኳሶችን አጥቂዎቹ መስፍን ታፈሰ እና አንተነህ ተፈራ ጥሩ ጥሩ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ዉጥናቸዉ ሰምሮ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዉ በጨዋታው በአዳማ ከተማ 1ለ0 ተሸንፈዋል።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ወልቂጤ ከተማ እና ሻሸመኔ ከተማ አቻ ሲለያዩ ፤ ኢትዮጵያ መድንም ከአስራ ሁለት ሳምንታት በኋላ ማሸነፍ ችሏል !!
Next Article የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀያ አንደኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የዝውውር ዜናዎችዜናዎችጅማ አባጅፋርቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

እያሱ ለገሰ ወደ ጅማ አባጅፋር አምርቷል!!

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 5 years ago
የአዳማ ከተማ የመጀመሪያው ዙር ጉዞ ሲዳሰስ
የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀያ ሰባተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ!
የአሰልጣኞች አስተያየት | ቅዱስ ጊዮርጊስ 3-2 ድሬደዋ ከተማ
ካፍ ለአባል ሀገራት እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች የሚያከፋፍለውን ዓመታዊ የገንዘብ ድጋፍ አሳደገ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?