By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ፋሲል ከነማ ከሀምበሪቾ ዱራሜ ጋር አቻ ሲለያይ ፤ ባህርዳር ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስም መርሐግብራቸዉን በተመሳሳይ በአቻ ዉጤት ፈፅመዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስባህርዳር ከተማሀምበሪቾ ድራሜየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማ

ፋሲል ከነማ ከሀምበሪቾ ዱራሜ ጋር አቻ ሲለያይ ፤ ባህርዳር ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስም መርሐግብራቸዉን በተመሳሳይ በአቻ ዉጤት ፈፅመዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በ21ኛዉ ሳምንት ሁለተኛ ዕለት ጨዋታ ፋሲል ከነማ ከሀምበሪቾ ዱራሜ ጋር ሁለት አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 10:00 ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ባህሩ ተካ ፊሽካ በጀመረዉ እና ቀዝቃዛ በሚባል የጨዋታ እንቅሰቃሴ በጀመረዉ ጨዋታ ባሳለፍነዉ ሳምንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ5ለ1 ሽንፈት ደርሶባቸዉ የነበሩት ሀምበሪቾዎች ገና በ11ኛዉ ደቂቃ ላይ ጨዋታዉን መምራት ጀምረዋል። በዚህም አብዱልሰላም ይሴፍ ከግራ መስመር በኩል ወደ ዉስጥ ገብቶ ያሻማዉን ኳስ የፋሲሉ ግብ ጠባቂ ሚካኤል ሳማኪ ራሱ ግብ ላይ አስቆጥሮ ሀምበሪቾዎች ገና በመባቻዉ ጨዋታዉን መምራት ጀምረዋል።

ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኃላ የጨዋታዉን የበላይነት በመዉሰድ የአቻነት ግብ ለማስቆጠር ተጭነዉ መጫወት የቀጠሉት አፄዎቹ በቃልኪዳን ዘላለም እና ሌሎችም ተጫዋቾች ዕድሎችን ከፈጠሩ በኋላ በ28ተኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም ከቀኝ በኩል ዮናታን ፍስሀ ያሻገረዉን ኳስ ያገኘዉ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ በቀጥታ ወደ ግብነት መቀየር ችሏል። ከሁለቱ ግቦች እና አልፎ አልፎ በሁለቱም በኩል ከሚደረጉ ኢላማቸዉን ያልጠበቁ ሙከራዎች ዉጭ ይህ ነዉ የሚባል ዕድል መፍጠር ያልቻሉት ሁለቱ ክለቦች አጋማሹን አንድ አቻ አገባደዋል።

- ማሰታውቂያ -

በሁለተኛው አጋማሽ ወደ ጨዋታዉ ለመመለስ በቶሎ መንቀሳቀስ የጀመሩት ሀምበሪቾዎች በ51ኛዉ ደቂቃ ላይ ዳግም ጨዋታውን መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ አግኝተዋል ፤ በዚህም በዕለቱ ድንቅ የነበረዉ አብዱልሰላም የሱፍ ከሚካኤል ሳማኪ ተጭኖ የቀማዉን ኳስ ወደ ግብነት በመቀየር ድንቅ ስራ ሰርቷል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ በ77ተኛዉ ደቂቃ ላይ የፋሲል ከነማዉ ተከላካይ ሀቢብ መሐመድ በረከት ወንድሙ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ በቀይ ካርድ ከሜዳ ሲወገድ ፤ ከደቂቃዎች በኃላም በድጋሚ ጫናቸዉ የበረታዉ ሀምበሪቾዎች በበረከት ወንድሙ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ አድርገዉ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች ። በዚህ ሂደት ቀጥሎ መደበኛ ዘጠና ደቂቃዉን በፈጀዉ ጨዋታ ላይም በ90+2 ደቂቃ ላይ ተቀይሮ የገባዉ ሸምሰዲን መሐመድ ከርቀት ድንቅ ግብ አስቆጥሮ አፄዎቹ ውድ የሆነ አንድ ነጥብ እንዲያገኙ አስችሏል።

በባህርዳር ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ መካከል የተደረገዉ የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ተጠናቋል ።

በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ መሪነት ምሽት 1:00 ሰዓት ሲል በጀመረዉ እና ድንቅ ፉክክር ባስመለከተዉ የምሽቱ ጨዋታ ገና ከመባቻዉ አንስቶ ሁለቱም ክለቦች የጨዋታዉን የበላይነት ለመቆጣጠር ሲጥሩ የነበረ ሲሆን በ5ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግን ባህርዳር ከተማ ድንቅ ሙከራ አድርገዋል። በዚህም አማካዩ ያብስራ ተስፋየ ከኋላ ክፍል የተላከለትን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም የግቡ ቋሚ ግን ኳሷን መልሶበታል።

በ29ነኛዉ ደቂቃ ላይ ተከላካዩ ፍራኦል መንግስቱ ከቀኝ መስመር በኩል ያሻማዉን ኳስ ሌላኛዉ ተከላካይ ፍሬዘር ካሳ ሞክሮ ወደ ዉጭ ሲወጣ ያንኑ ኳስም ማዕዘን ሆኖ ቸርነት ጉግሳ የማዕዘን ኳሱን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ የአቻነት ግብ ፍለጋ የቀጠሉት ፈረሸኞቹ ሞሰስ ኦዶ ከማዕዘን ቢኒያም በላይ ያሻማውን ኳስ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ያሬድ እና መሳይ ኳሷን ተረባርበዉ እንደምንም አውጥተዋል።

በተደጋጋሚ የፈረሰኞቹን የግብ ክልል ሲፈትሹ የነበሩት የጣና ሞገዶቹ በፍሬዘር ካሳ አማካኝነት ከግራ መስመር በኩል ከቆመ ኳስ የተሻገረዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክረዉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል ። ከዕረፍት መልስ በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ሁለቱም ቡድኖች ቀይረዉ ወደ ሜዳ በማስገባት የጨዋታውን የበላይነት ለመዉሰድ ሲጥሩ የተስተዋለ ሲሆን ፤ ባህርዳር ከተማዎች በይበልጥ ወደ ራሳቸዉ የግብ ክልል አፈግፍገው በጥብቅ መከላከል እና በመልሶ ማጥቃት በቸርነት በኩል ባመዘነ እንቅስቃሴ ለመጫወት ሲጥሩ ፤ በተቃራኒው ፈረሰኞቹ ግን ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸዉን የአቻነት ግብ ለማግኘት ሲጥሩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ ተስተውሏል።

በ75ተኛዉ ደቂቃ ላይ ቸርነት ጉግሳ በድጋሚ ከግራ መስመር ሳጥን ውስጥ ከገባ በኋላ በቀጥታ ወደ ግብ ድንቅ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ኳሷ በግቡ ቋሚ አጠገብ ለጥቂት ወጥታለች።

በ89ነኛዉ ደቀቃ ዳግማዊ አርአያ ፍሬዘር ካሳን አታሎ ያገኘዉን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ሲሞክር ግብ ጠባቂዉ ሲመለስ የተገኘዉን ኳስ በቅርበት የነበረዉ ታምራት እያሱ ሞከሮ የነበረ ቢሆንም ተከላካዮች ተረባርበዉ አፅድተዋል። በ94ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር በኩል ተከላካዩ አማኑኤል ተርፉ ያሻማውን ኳስ ሳጥን ውስጥ ያገኘዉ አማኑኤል ኤረቦ በጭንቅላቱ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን አቻ አድርጎ ፤ መርሐግብሩም አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ዉጤት ፍፃሜዉን አጊኝቷል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ሲችል ፤ በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ የተከወነዉ የምሽቱ ጨዋታም በአቻ ዉጤት ፍፃሜዉን አጊኝቷል !!
Next Article ወልቂጤ ከተማ እና ሻሸመኔ ከተማ አቻ ሲለያዩ ፤ ኢትዮጵያ መድንም ከአስራ ሁለት ሳምንታት በኋላ ማሸነፍ ችሏል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንዜናዎች

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ጥያቄ አላቀረበችም”አቶ ባህሩ ጥላሁን 

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 3 years ago
የ2011 ኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 4ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሳምንት ጨዋታዎች በቀጥታ ውጤት /LIVESCORE/ ይከታተሉ
አቡበከር ናስር የእውቅና ሽልማት ተበረከተለት
“የኢትዮጵያ ቡናን ማልያ ለብሼ እንድጫወት ትልቁ ምክንያት የሆነኝ በቃላት የማይገለፀው ደጋፊው ነው”ወንድሜነህ ደረጀ (ኢት.ቡና)
በ2 ሰከንዶች ሪከርድ ባለመስበሩ ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ አምልጦታል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?