By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ሲችል ፤ በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ የተከወነዉ የምሽቱ ጨዋታም በአቻ ዉጤት ፍፃሜዉን አጊኝቷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የጨዋታ ዘገባየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችሀዋሳ ከተማድሬዳዋ ከተማኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ሲችል ፤ በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ የተከወነዉ የምሽቱ ጨዋታም በአቻ ዉጤት ፍፃሜዉን አጊኝቷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

ቀን 10 ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ቢኒያም ወርቅአገኘሁ ፊሽካ በጀመረዉ ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ የተሻለ ብልጫ የነበራቸዉ እና የተወሰኑ ጫናዎችን መፍጠር የቻሉት ባንኮች በ19ነኛዉ ደቂቃ ላይ ሱለይማን ሀሚድ ከቀኝ መስመር በኩል ያሻማዉን ኳስ ባሲሩ ዑመር ወደ ግብ ቢሞክርም የግብ ዘቡ ኳሷን ተቆጣጥሯል ።

ከዚች ተጠቃሽ ሙከራ በኋላ አሁንም የጨዋታዉን የመሐል ሜዳ ብልጫ በመዉሰድ መጫወት የቀጠሉት ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች በ23ተኛዉ ደቂቃ ላይ በድጋሚ ከቀኝ መስመር ሱለይማን ባሻገረዉ እና ሲሞን ፒተር በቀጥታ ወደ ግብ በሞከረዉ የጭንቅላት ኳስ ድንቅ ሙከራ ማድረግ ችለዉ ነበር ፤ በዚህ ሂደት በቀጠለው ጨዋታ አጋማሹ ሊገባደድ ስድስት ያክል ደቂቃዎች ሲቀሩ አጠቃላይ በእንቅስቃሴ ብልጫ የተወሰደበት ሀዋሳ ከተማ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

በዚህም በ39ነኛዉ ደቂቃ ላይ አቤነዘር ዮሐንስ ያቀበለዉን ኳስ ፈጣኑ አጥቂ አሊ ሱለይማን የግል ክህሎቱን ጭምር በመጠቀም ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። በእንቅስቃሴ ረገድ የተሻሉ ቢሆንም ሳጥን ውስጥ ግን ስል መሆን ያልቻሉት ባንኮች በሀብታሙ ሸዋለም እና ባሲሩ ዑመር ድንቅ ሙከራዎችን ማድረግ ቢችሉም ግብ ጠባቂዉ ፂዮን መርዕድ ኳሷቹን ተቆጣጥሯል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስ ብልጫቸዉን ያስቀጠሉት ባንኮች በ50ኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ግብ አግኝተዋል። በዚህም ከግራ በኩል የተገኘዉን የቅጣት ምት ኳስ ፋዓድ ፈረጃ ሲመታዉ ግብ ጠባቂዉ ፅዮን ኳሱን ሲመልሰዉ ያገኘዉ ሳይመን ፒተር ኳሷን ወደ ግብነት መቀየር ችሏል። አጋማሹ በተጀመረ በአምስት ደቂቃ ውስጥ አቻ መሆን የቻሉት ባንኮች ከደቂቃዎች በኋላ በ65ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከመመራት ወደ መሪነት መሸጋገር ችለዋል። በዚህም ፋዓድ ፈረጃ ያቀበለዉን ኳስ ኪቲካ ጀማ ወደ ግብነት ቀይሯል።

ግብ ያስቆጥሩ እንጅ የጨዋታዉ ደቂቃ እየገፋ በሄደ ቁጥር እየተቀዛቀዙ የሄዱት ሀዋሳ ከተማዎች በእንደ እዮብ አለማየሁ እና አሊ ሱለይማንን በመሳሰሉ ተጫዋቾች ጥሩ ሙከራዎችን ማድረግ ቢችሉም ውጥናቸዉ ሰምሮ የአቻነት ግብ ማግኘት ሳይችሉ ጨዋታዉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊነት ተጠናቋል።

በበርካታ ደጋፊዎች ድባብ ታጅቦ በተከናወነው የምሽቱ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ እና ወላይታ ዲቻ አቻ ተለያይተዋል ።

በዋና ዳኛ ሀይለየሱስ ባዘዘዉ ፊሽካ ምሽት አንድ ሰዓት ሲል በጀመረዉ እና ተመጣጣኝ የጨዋታ ፉክክር በተመለከትንበት ጨዋታ ወላይታ ዲቻ በቀዳሚነት ሙከራ ማድረግ ችሎ ነበር ፤ በዚህም አብነት ደምሴ ከባየ ገዛኸኝ የተቀበለዉን ኳስ ሳጥን ውስጥ በቀጥታ ወደ ግብ ቢሞክርም ኳሱ በአናት ላይ ወደ ዉጭ ወጥቷል።

በተለይ የጨዋታዉን የእንቅስቃሴ ሚዛን ወደ መስመር በኩል በመዉሰድ እና የተሻለ ብልጫ በመዉሰዱ ሰገድ የተሻሉ የነበሩት ድሬዳዋ ከተማዎች በግራ መስመር በኩል መሐመድ አብዱለጢፍ ያሻማዉን ኳስ ሱራፌል በጭንቅላቱ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ሙከራዉ ግን ዉጤታማ ሳይሆን ቀርቷል።

በ44ተኛዉ ደቂቃ ላይ ባየ ገዛኸኝ ከኋላ ክፍል ከአዛርያ በረዥሙ የተሻገረለትን ኳስ ከተቆጣጠረ በኀላ በቀጥታ ኳሷን ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኳሷ ለጥቂት በግቡ ቋሚ አጠገብ ወደ ዉጭ ወጥታለች። ከዕረፍት መልስ ጨዋታዉን በጥቂቱም ቢሆንም መቆጣጠር የቻሉት ድሬዳዋ ከተማዎች በ55ተኛዉ ደቂቃ ላይ መሪ መሆን ችለዋል ፤ በዚህም ካርሎስ ዳምጠዉ ላይ የተሰራዉን ጥፋት ተከትሎ የተገኘዉን ፍፁም ቅጣት ምት ራሱ ተጫዋቹ ወደ ግብነት መቀየር ችሏል።

ከአበባየሁ ሀጂሶ የተቀበለዉን ኳስ ብዙዓየሁ ሰይፈ የግል ክህሎቱን ተጠቅሞ ተጫዋቾችን አታሎ በማለፍ ድንቅ ግብ በማስቆጠር ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል። የአቻነት ግብ ከተቆጠረ በኋላ በእንቅስቃሴዉ ሁለቱም ክለቦች ቶሎ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመድረስ ዕድሎችን ለመፍጠር እና ግብ ለማስቆጠር ሲያደርጉት የነበረዉ ጥረት ሳይሳካ ቀርቶ መርሐግብሩ አንድ አቻ በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀያኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ!
Next Article ፋሲል ከነማ ከሀምበሪቾ ዱራሜ ጋር አቻ ሲለያይ ፤ ባህርዳር ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስም መርሐግብራቸዉን በተመሳሳይ በአቻ ዉጤት ፈፅመዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስ

ስደተኛውና ተጠባቂው የሸገር ደርቢ ነገ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዳማው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 2 years ago
የጨዋታ ዘገባ | የአለልኝ አዘነ የመጨረሻ ግብ ለሀዋሳ ሶስት ነጥብ አስገኝቷል
የሊግ ካምፓኒው 2000 ደጋፊ እንዲገባ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ሆነ
“ወደ ሩጫው አስገድዶ ያስገባኝ ለቀነኒሳ ያለኝ አድናቆትና ፍቅር ነው፤ምኞቴ በለንደኑ የዓለም ሻምፒዮና ሀገሬን ወክዬ ውጤታማ ማድረግ ነው”አትሌት ልዑል ገ/ስላሴ ከኦታዋ
ዝውውር | አቅሌሲያስ ግርማ ለመከላከያ ፊርማውን አኑሯል 
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?