By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በተከታታይ ጨዋታዎች ነጥብ ጥለዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችባህርዳር ከተማአርባምንጭ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በተከታታይ ጨዋታዎች ነጥብ ጥለዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 3 years ago
Share
SHARE

በሊጉ የ22ኛ ሳምንት ሶስተኛ መርሀግብር ባህርዳር ከተማን ከአርባምንጭ ከተማ አገናኝቶ 2 – 2 በሆነ ውጤት ፍፃሜውን አግኝቷል ።

በጨዋታው በሁለቱም ክለቦች በኩል ካለፈው ሳምንት ጨዋታዎቻቸው አንድ አንድ ለውጦችን አድርገዋል ።

በባህርዳር ከተማ በኩል ከኢትዮጵያ መድኅን አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ላይ ከነበረው ምርጥ አስራአንድ በአምስተኛ ቢጫ ምክንያት ባልተሰለፈው አለልኝ አዘነ ምትክ ፍቅረሚካኤል አለሙ ሲሰለፍ በአርባምንጭ ከተማ በኩል በሳምንቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ በተረቱበት ጨዋታ ላይ ከነበረው የመጀመሪያ አሰላለፍ እንዳልካቸው መስፍንን በአቡበከር ሻሚል ተክተው ገብተዋል ።

የዘጠኝ ሰዓቱ ጨዋታ ገና በጊዜ ነበር በሁለቱም በኩል ግቦች የተስተናገዱበት ነበር ። በሶስተኛው ደቂቃ ላይ የጣና ሞገዶቹ በፍራኦል መንግስቱ አማካኝነት ቀዳሚ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋል ።

- ማሰታውቂያ -

ከግቡ በርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት የግራ መስመሩ ተከላካይ ፍራኦል መንግስቱ ወደ አርባምንጭ ከተማ የግብ ክልል ሲያሻግረው የአርባምንጭ ከተማው ግብ ጠባቂ የሰአት አጠባበቅ ስህትት ታክሎበት ኳስ እና መረብ ተገናኝተዋል ።

በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የሚመሩት አርባምንጭ ከተማዎች ከአፍታ በኋላ መልስ የሰጡበትን ግብ አግኝተዋል ። አማካዩ እንዳልካቸው መስፍን ከግራ መስመር አቅጣጫ የተገኘውን የቅጣት ምት ልክ እንደ ፍራኦል ሁሉ ለቡድን አጋሮቹ ያሻገረው ኳስ በ5ኛው ደቂቃ ከመረብ አርፏል ።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ ጨዋታው ልክ እንደ አጀማመሩ መቀጠል አልቻለም ።

ሁለቱም ክለቦች እየተፈራረቁ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ቢጥሩም ሌላ ግብ ለማከል ሳይችሉ አጋማሹን ለማጠናቀቅ ተገደዋል ።

በ16ኛው ደቂቃ ላይ ፍፁም ጥላሁን ከቀኝ መስመር ያሻገረውን ኳስ ፉአድ ፈረጃ ማግኘት ችሎ የነበረ ቢሆንም ወደ ግብ የመታው ኳስ ጠንካራ ባለመሆኑ በቀላሉ በግብ ጠባቂው ተይዟል ።

በአርባምንጭ ከተማ በኩል በተለይም በቀኝ መስመር በኩል በሚሻገሩ ኳሶች ኳስ እና መረብን ለማገናኘት የተደረጉ ጥረቶች ስኬታማ አልነበሩም ።

ቀድመው ከተቆጠሩት ግቦች በኋላም ሌላ ጠንካራ የግብ ሙከራም ሆነ ግብ ሳይታይ የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቋል ።

በጨዋታው የሁለተኛ አጋማሽ በማጥቃቱ ላይ አደም አባስን በዱሬሳ ሹቢሳ ተክተው የገቡት ባህርዳር ከተማዎች የተሻለ ጫና ፈጥረው ለመጫወት ችለዋል ።

በአርባምንጭ ከተማ በኩል ረጃጅም ኳሶችን በመጠቀም በፊት መስመር ለሚገኘው አህመድ ሁሴን ኳሶችን በማድረስ የግብ ዕድል ለመፍጠር በተወሰኑ አጋጣሚዎች ጥረቶችን አድርገዋል ።

በ57ኛው ደቂቃ ላይ መሳይ አገኘሁ በረጅም ወደ ሳጥን ያሻገረውን ኳስ በአደም አባስ እና ፉአድ ፈረጃ በኩል አልፎ ለሀብታሙ ታደሰ የደረሰውን ኳስ አጥቂው ሳይጠቀምበት ቀርቷል ።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላም የጣና ሞገዶቹ እጅግ ለግብ የቀረበ አጋጣሚ መፍጠር ቢችሉም በማይታመን መልኩ ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል ። በፈጣን መልሶ ማጥቃት ይዘው የሄዱትን ኳስ ሀብታሙ ታደሰ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ሆኖ ለአደም አባስ አቀብሎት የነበረ ቢሆንም ከግቡ በጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ሆኖ ከመኮንን መርዶክዮስ የተፋጠጠው አደም አባስ ኳሱን ከግቡ አናት በላይ ልኮታል ።

በአጋማሹ በተለይም ሀብታሙ ታደሰ ወደ ኋላ ተመልሶ ከቡድን አጋሮቹ ጋር በሚያደርገው አንድ ሁለት ቅብብል ለሌሎች ተጫዋቾች የግብ ዕድሎች ለማመቻቸት ሲጥር ተተስተውሏል ።

በ68ኛው ደቂቃ ላይም ባህርዳር ከተማዎች ዳግም መሪ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋል ። አሸናፊ ፊዳ በሀብታሙ ታደሰ በተደረገበት ጫና ወደ ኋላ መልሶ ለመኮንን መርዶክዮስ ያደረሰውን ኳስ መኮንን መልሶ ለአሸናፊ ለማቀበል በሚያደርገው ጥረት ወቅት ሀብታሙ ኳሱን አግኝቶ ለፉአድ ፈረጃ አቀብሎት 10 ቁጥር ለባሹ ፉአድ ኳስ እና መረብን አገናኝቷል ።

በመጀመሪያው አጋማሽ ግብ ተቆጥሮባቸው አቻ ለመሆን ብዙ ደቂቃ ያልወሰደባቸው አዞዎቹ በዚህኛው አጋጣሚም ከስምንት ደቂቃዎች በኋላ ዳግም አቻ ሆነዋል ። የፊት አጥቂው አህመድ ሁሴን ከበላይ ገዛኸኝ በግሩም ዕይታ የደረሰውን ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ በመምታት በታፔ አልዛየር መረብ ላይ አሳርፎታል ።

በቀጣዮቹ የጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች በተለይም በባህርዳር ከተማ በኩል ተጭነው በመጫወት ሌላ ግብ ለማግኘት ያደረጓቸው ጥረቶች ውጤታማ መሆን ሳይችሉ ቀርተዋል ።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በተጨማሪ ደቂቃዎች ላይ ፉአድ ፈረጃ ከሳጥኑ ጫፍ ላይ ሆኖ ወደ ግብ ያደረገው ሙከራ በግብ ጠባቂው ተመልሷል ።

በመጨረሻም ጨዋታው በ2 – 2 ውጤት ተጠናቋል ።

በ23ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ግንቦት 1(ማክሰኞ) ከቀኑ 9:00 ጀምሮ ባህርዳር ከተማ ከኢትዮጵያ ቡና ሲጫወት በዕለቱ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ አርባምንጭ ከተማ ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ ጣፋጭ ድል አስመዝግበዋል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ ቡና እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችሀዋሳ ከተማLIVESCORE

ወላይታ ድቻ ከ ሀዋሳ ከተማ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 5 years ago
አርቢትር ኃይለየሱስ ባዘዘው ተቀጣ መባሉ ቁጣን ቀስቅሷል
ዋልያዎቹ ዝግጅታቸውን በካሜሩን ያደርጋሉ !!
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ጥያቄ አላቀረበችም”አቶ ባህሩ ጥላሁን 
ብሩክ እንዳለ፣ ዳንላንድ ኢብራሂም፣ ኤልያስ አህመድ እና ሐይደር ሸረፋ የጨዋታ እገዳ ሲጣልባቸው በክለቦች ኢትዮጵያ ቡና፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ሀዲያ ሆሳዕና እና ወልዋሎ የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?